መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሬ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ሳዲሁን የደሞዝ ማሻሻያው ሰው ተኮር በመሆኑ በአሠሪው መሥሪያ ቤቶች አመራርና ፋይናንስ አካላትን ባሳተፈ መልኩ የጋራ ምክክር ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
የኮሬ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ፣ የግብርና መምሪያ ኃላፊና የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አስታረቀኝ አንደባ እንደተናገሩት አመራሩ ሁልጊዜ ዝግጁ መሆን እንዳለበት አስታውሰው የመዋቅር ስፋትና ጥበት በየጊዜው እየተጠና ችግሮች እየተፈታ ይሄዳል በማለት በዋናነት ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት ለህብረተሰቡ መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል።
በመድረኩም ከደሞዝና የውሎ አበል ማሻሻያ ጋርም በተያያዘ ኢኮኖሚን በጥረት ሠርቶ ማምጣት እንደሚጠበቅ አስረድተዋል፡፡
ከተሳታፊዎች መካከል አቶ አለማየሁ አሰፋ፣ አቶ ወረደ ወርቁና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት በደሞዝ ማሻሻያ ትግበራ የሲቪል ሰርቪስና ሰው ሀብት በጥንቃቄ መሥራትና የአመራሩም ክትትል እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።
ዘጋቢ፡ ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ