መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሬ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ሳዲሁን የደሞዝ ማሻሻያው ሰው ተኮር በመሆኑ በአሠሪው መሥሪያ ቤቶች አመራርና ፋይናንስ አካላትን ባሳተፈ መልኩ የጋራ ምክክር ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
የኮሬ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ፣ የግብርና መምሪያ ኃላፊና የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አስታረቀኝ አንደባ እንደተናገሩት አመራሩ ሁልጊዜ ዝግጁ መሆን እንዳለበት አስታውሰው የመዋቅር ስፋትና ጥበት በየጊዜው እየተጠና ችግሮች እየተፈታ ይሄዳል በማለት በዋናነት ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት ለህብረተሰቡ መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል።
በመድረኩም ከደሞዝና የውሎ አበል ማሻሻያ ጋርም በተያያዘ ኢኮኖሚን በጥረት ሠርቶ ማምጣት እንደሚጠበቅ አስረድተዋል፡፡
ከተሳታፊዎች መካከል አቶ አለማየሁ አሰፋ፣ አቶ ወረደ ወርቁና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት በደሞዝ ማሻሻያ ትግበራ የሲቪል ሰርቪስና ሰው ሀብት በጥንቃቄ መሥራትና የአመራሩም ክትትል እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።
ዘጋቢ፡ ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ