መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሬ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ሳዲሁን የደሞዝ ማሻሻያው ሰው ተኮር በመሆኑ በአሠሪው መሥሪያ ቤቶች አመራርና ፋይናንስ አካላትን ባሳተፈ መልኩ የጋራ ምክክር ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
የኮሬ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ፣ የግብርና መምሪያ ኃላፊና የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አስታረቀኝ አንደባ እንደተናገሩት አመራሩ ሁልጊዜ ዝግጁ መሆን እንዳለበት አስታውሰው የመዋቅር ስፋትና ጥበት በየጊዜው እየተጠና ችግሮች እየተፈታ ይሄዳል በማለት በዋናነት ወጪ ቆጣቢ አገልግሎት ለህብረተሰቡ መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል።
በመድረኩም ከደሞዝና የውሎ አበል ማሻሻያ ጋርም በተያያዘ ኢኮኖሚን በጥረት ሠርቶ ማምጣት እንደሚጠበቅ አስረድተዋል፡፡
ከተሳታፊዎች መካከል አቶ አለማየሁ አሰፋ፣ አቶ ወረደ ወርቁና ሌሎችም በሰጡት አስተያየት በደሞዝ ማሻሻያ ትግበራ የሲቪል ሰርቪስና ሰው ሀብት በጥንቃቄ መሥራትና የአመራሩም ክትትል እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።
ዘጋቢ፡ ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ