የቡርጂ ዞን ምክር ቤት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾመ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የቡርጂ ዞን ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዙር 3ኛ የሥራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ አጽደቀ።
የቡርጂ ዞን ም/ቤት አፌ ጉባኤ ወ/ሮ ወለቱ ዋዮ ምክር ቤቱ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ስልጣን መሠረት በማድረግ በተጠራው አስቸኳይ ጉባኤ የም/ቤቱ አባላት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የ2017 የሥራ ዘመን የምክር ቤቱ አጀንዳ በሙሉ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን የክልሉ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ለምክር ቤቱ የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በእጩነት የቀረቡትን አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው እንዲመሩ በሙሉ ድምፅ አፀድቋል።
የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው የተሾሙት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ በም/ቤቱ ፊት ቀርበው ዞኑን በቅንነት እና በታማኝነት ለማገልገል ቃለ መሐላ ፈጽመዋል።
በጉባኤው ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተማ አስተዳደር የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግለዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተሳትፈውበታል ።
ዘጋቢ: ወርቅአገኘሁ ወልደየስ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የወባ በሽታ ስርጭትን የመከላከልና የመቆጣጠርን ጉዳይ ቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ አስታወቀ
አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ተገልጋዩን ለማርካት እየሰራ መሆኑን የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አስታወቀ
የባስኬቶ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ አመት የሥራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን አካሂዷል