የቡርጂ ዞን ምክር ቤት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾመ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የቡርጂ ዞን ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዙር 3ኛ የሥራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ አጽደቀ።
የቡርጂ ዞን ም/ቤት አፌ ጉባኤ ወ/ሮ ወለቱ ዋዮ ምክር ቤቱ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ስልጣን መሠረት በማድረግ በተጠራው አስቸኳይ ጉባኤ የም/ቤቱ አባላት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የ2017 የሥራ ዘመን የምክር ቤቱ አጀንዳ በሙሉ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን የክልሉ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ለምክር ቤቱ የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በእጩነት የቀረቡትን አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው እንዲመሩ በሙሉ ድምፅ አፀድቋል።
የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው የተሾሙት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ በም/ቤቱ ፊት ቀርበው ዞኑን በቅንነት እና በታማኝነት ለማገልገል ቃለ መሐላ ፈጽመዋል።
በጉባኤው ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተማ አስተዳደር የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግለዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተሳትፈውበታል ።
ዘጋቢ: ወርቅአገኘሁ ወልደየስ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ