የቡርጂ ዞን ምክር ቤት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾመ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የቡርጂ ዞን ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዙር 3ኛ የሥራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ አጽደቀ።
የቡርጂ ዞን ም/ቤት አፌ ጉባኤ ወ/ሮ ወለቱ ዋዮ ምክር ቤቱ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ስልጣን መሠረት በማድረግ በተጠራው አስቸኳይ ጉባኤ የም/ቤቱ አባላት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የ2017 የሥራ ዘመን የምክር ቤቱ አጀንዳ በሙሉ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን የክልሉ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ለምክር ቤቱ የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በእጩነት የቀረቡትን አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው እንዲመሩ በሙሉ ድምፅ አፀድቋል።
የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው የተሾሙት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ በም/ቤቱ ፊት ቀርበው ዞኑን በቅንነት እና በታማኝነት ለማገልገል ቃለ መሐላ ፈጽመዋል።
በጉባኤው ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተማ አስተዳደር የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግለዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተሳትፈውበታል ።
ዘጋቢ: ወርቅአገኘሁ ወልደየስ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ