የቡርጂ ዞን ምክር ቤት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾመ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የቡርጂ ዞን ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዙር 3ኛ የሥራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ በሙሉ ድምጽ ተቀብሎ አጽደቀ።
የቡርጂ ዞን ም/ቤት አፌ ጉባኤ ወ/ሮ ወለቱ ዋዮ ምክር ቤቱ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ስልጣን መሠረት በማድረግ በተጠራው አስቸኳይ ጉባኤ የም/ቤቱ አባላት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ ጠይቀዋል።
የ2017 የሥራ ዘመን የምክር ቤቱ አጀንዳ በሙሉ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን የክልሉ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ለምክር ቤቱ የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በእጩነት የቀረቡትን አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው እንዲመሩ በሙሉ ድምፅ አፀድቋል።
የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው የተሾሙት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ በም/ቤቱ ፊት ቀርበው ዞኑን በቅንነት እና በታማኝነት ለማገልገል ቃለ መሐላ ፈጽመዋል።
በጉባኤው ከክልል፣ ከዞን፣ ከወረዳ እና ከከተማ አስተዳደር የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግለዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተሳትፈውበታል ።
ዘጋቢ: ወርቅአገኘሁ ወልደየስ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ