ምክር ቤቱ በነበረው ቆይታ የዞኑን ዋና አስተዳዳሪ ሹመት መርምሮ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል።
የባስኬቶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ማርቆስ ልፋቱ፤ ጉባኤው የህዳሴ ግድባችን ተጠናቆ አገልግሎት መሥጠት በጀመረበት ማግስት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዱፄ ታምሩ፤ ዞኑን በዋና አስተዳዳሪነት እንዲያገለግሉ እጩ ዶ/ር ሳሙኤል ደሳለኝን በዕጩነት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
የምክር ቤቱ አባላት በቀረቡት ዕጩ አስተዳዳሪ ዙሪያ ሀሳብ አስተያየታቸውን ሰጥተው በሙሉ ድምፅ አፅድቀዋል።
የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እጩ ዶ/ር ሳሙኤል ደሳለኝ በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ባደረጉት ንግግር በዞኑ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ሠላምና ጸጥታ ዘርፎች ላይ የታቀዱ ተግባራትን ለማሳካት በፅናት ይሰራል ብለዋል።
በዞኑ የሚገኘውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ጥቅም ላይ ለማዋል ያለ ልዩነት አካታች አሰራርን ለመከተል ልዩ ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ