ምክር ቤቱ በነበረው ቆይታ የዞኑን ዋና አስተዳዳሪ ሹመት መርምሮ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል።
የባስኬቶ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ማርቆስ ልፋቱ፤ ጉባኤው የህዳሴ ግድባችን ተጠናቆ አገልግሎት መሥጠት በጀመረበት ማግስት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዱፄ ታምሩ፤ ዞኑን በዋና አስተዳዳሪነት እንዲያገለግሉ እጩ ዶ/ር ሳሙኤል ደሳለኝን በዕጩነት ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
የምክር ቤቱ አባላት በቀረቡት ዕጩ አስተዳዳሪ ዙሪያ ሀሳብ አስተያየታቸውን ሰጥተው በሙሉ ድምፅ አፅድቀዋል።
የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እጩ ዶ/ር ሳሙኤል ደሳለኝ በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ባደረጉት ንግግር በዞኑ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ሠላምና ጸጥታ ዘርፎች ላይ የታቀዱ ተግባራትን ለማሳካት በፅናት ይሰራል ብለዋል።
በዞኑ የሚገኘውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ጥቅም ላይ ለማዋል ያለ ልዩነት አካታች አሰራርን ለመከተል ልዩ ትኩረት የሚሰጠው መሆኑን አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ