በቫሌንሽያ ግማሽ ማራቶን አትሌት ዩሚፍ ቀጄልቻ አሸነፈ
በስፔን ቫሌንሽያ በተካሄደው በወንዶች የግማሽ ማራቶን አትሌት ዩሚፍ ቀጄልቻ አሸንፏል።
አትሌት ዩሚፍ ቀጄልቻ 58 ደቂቃ ከ02 ሴኮንድ በመግባት ነው ውድድሩን በቀዳሚነት ያጠናቀቀው።
የርቀቱ የዓለም ክብረወሰን ባለቤት የሆነው አትሌት ዮሚፍ የባለፈው ዓመት የቫሌንሽያ ግማሽ ማራቶን ውድድርም አሸናፊ እንደነበር ይታወሳል።
በሴቶች የግማሽ ማራቶን ውድድር ደግሞ አትሌት ፎቲዬን ተስፋዬ 2ኛ ሆና አጠናቃለች።
አትሌቷ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 1 ሰዓት ከ05 ደቂቃ ከ11 ሴኮንድ ፈጅቶባታል።
ውድድሩን ኬንያዊቷ አትሌት አግኔስ ንጌቲች በቀዳሚነት አጠናቃለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ