በቫሌንሽያ ግማሽ ማራቶን አትሌት ዩሚፍ ቀጄልቻ አሸነፈ
በስፔን ቫሌንሽያ በተካሄደው በወንዶች የግማሽ ማራቶን አትሌት ዩሚፍ ቀጄልቻ አሸንፏል።
አትሌት ዩሚፍ ቀጄልቻ 58 ደቂቃ ከ02 ሴኮንድ በመግባት ነው ውድድሩን በቀዳሚነት ያጠናቀቀው።
የርቀቱ የዓለም ክብረወሰን ባለቤት የሆነው አትሌት ዮሚፍ የባለፈው ዓመት የቫሌንሽያ ግማሽ ማራቶን ውድድርም አሸናፊ እንደነበር ይታወሳል።
በሴቶች የግማሽ ማራቶን ውድድር ደግሞ አትሌት ፎቲዬን ተስፋዬ 2ኛ ሆና አጠናቃለች።
አትሌቷ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 1 ሰዓት ከ05 ደቂቃ ከ11 ሴኮንድ ፈጅቶባታል።
ውድድሩን ኬንያዊቷ አትሌት አግኔስ ንጌቲች በቀዳሚነት አጠናቃለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ