አርሶ አደሩ በእንሰት ተክል የምግብ ዋስትናውን በማረጋገጥ የኢኮኖሚ አቅሙን እንድያሳድግ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
ሀዋሳ፣ ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ)በአሪ ዞን ዎባ አሪ ወረዳ አርሶ አደሩ የእንሰት ተክልን በማልማት ከዘርፉ ይበልጥ ተጠቃሚ እንዲሆን ስልጠና ተሰጥቷል
የትኛውንም የአየር ንብረት ለውጥ የመቋቋም ከፍተኛ አቅም ያለው የእንሰት ተክል በዎባ አሪ ወረዳ በየአመቱ ከ180 ሄ/ር በላይ በአዲስ ተከላ እንደሚለማ የገለፁት የወረዳዉ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቢሻዉ መካሪ ከሙሩፅ ጎይቶም የእሸት ቡና መፈልፈያ ኢንድስትሪ ባለቤት ጋር በመተባበር አርሶ አደሩ በአከባቢዉ ካለዉ ሰፊ የእንሰት ምርት በኢኮኖሚ አቅማቸዉን እንዲያሳድጉ ለሴት አርሶ አደሮች ስልጠናዉ መሰጠቱን ገልፀዋል፡፡
የሙሩፅ ጎይቶም የእሸት ቡና መፈልፈያ ኢንድስትሪ ኃላፊ አቶ ማሙሽ አልዬ በበኩላቸዉ አከባቢዉ ላይ ካለዉ የእንሰት ዝርያ የተሻለ የእንሰት ዝርያን ከምዕራብ አሪሲ በማምጣትና አከባቢዉ ላይ በማልማት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰሩ እንዳለ አስረድተዋል፡፡
የዎባ አሪ አርሶ አደሮች የእንሰት ተክልን ከአምቾና ከቂጣ ባለፈ የተለያዩ የምግብ ዓይነቶችን አዘጋጅተው ለራሳቸው ምግብነትም ሆነ ለገበያ አቅርበው በመሸጥ ተጠቃሚ እንዲሆን ስልጠና መሰጠቱን ተገልጿል፡፡
በወረዳዉ የዲራመርና የቦይካ ቀበሌ አርሶ አደር ሚሚ ስዩምና ገሺዬ ዳሽዬ በጋራ በሰጡት አስተያየት ከዚህ ቀደም እንሰቱን በመቆፈር ተፍቆ ቂጣ ብቻ እንደሚያዘጋጁና አሁን ግን በስልጠናዉ ቡላና ሌሎች የምግብ አዘገጃጀቶችን ግንዛቤ በማግኘታቸዉ በቀጣይ በዘርፉ በተሻለ ሁኔታ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ ፡ በናወርቅ መንግስቱ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳዳር ጥያቄዎች በዘላቂነት እንዲመለሱ ከየትኛውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኧሌ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ገለፀ
መንግስት የደን ጭፍጨፋን በመከላከል የአየር ሚዛንን ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ውስጥ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ እስታውቀ
የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እንዲያስችል ዞኑ የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ