”የትምህርት ጥራትና የተማሪዎችን ውጤት እናሻሽላለን” በሚል መሪ ቃል በ2017 ትምህርት ዘመን የተሻለ አስተዋጽኦ ላበረከቱ መምህራንና የጽህፈት ቤቱ ባለሙያዎች የዕውቅና ሽልማት መርሃ-ግብር በጌዴኦ ዞን የወናጎ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አካሂዷል፡፡
በመድረኩ የወናጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ እጅጉ እንደገለፁት፤ በሥራ አፈፃፀም ግንባር ቀደም የሆኑትን መምህራንና የጽ/ቤቱን ባለሙያዎች ለማበረታታትና ከወትሮው በላቀ ደረጃ በሥራ እንዲተጉ ታስቦ የተዘጋጀ የዕውቅና ሽልማት መርሃ-ግብር ነው፡፡
ባለፉት ጊዜያት በትምህርት ዘርፍ የተስተዋሉ ክፍተቶችን በማረም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ከባለድርሻዎች ጋር በመቀናጀት በትኩረት እየሠሩ መሆናቸውን አቶ አበበ ገልፀዋል፡፡
የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍሌ፤ ጥራት ያለውን ትምህርት ለዜጎች ለማድረስ እየተጉ ያሉትን ባለድርሻዎች ማበረታታት የትምህርትን ስብራት ለመጠገን ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ጥሩ ሰነ ምግባር የተላበሰ ፍሬያማ ትውልድ ለመፍጠር አሁን ላይ ዋጋ በመክፈል በቅንነትና በታማኝነት የሚሰጠውን ኃላፊነት በመወጣት ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አቶ ዘማች አሳስበዋል፡፡
የትምህርት ለውጥ የሚመጣው በአንድ ጀንበር ባለመሆኑ የትምህርት ሥራችን ዋነኛ ተዋናዮች የትኛውንም ዋጋ በመክፈል ጥራት ያለውን ትምህርት ለዜጎች የማድረስ ሥራ በብቃትና ትጋት መሥራት እንደሚገባቸው አቶ ዘማች አክለዋል።
አሁን ላይ ትልቅ ደረጃ ደርሰው ሀገርንና ህዝብን እያገለገሉ ያሉትን ምሁራን ያፈሩ መምህራን መሆናቸውን ታሳቢ በማድረግ በቀጣይም የትምህርትን ሥራ ለማሳለጥ የተዘጋጀ የዕውቅናና ሽልማት ፕሮግራም ማዘጋጀታቸውን የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መኮንን ጪጩ አስታውቀዋል፡፡
የትምህርት ባለሙያዎች በቀጣይ የትምህርት ሥራ ወቅት ያላቸውን እውቀትና ጉልበት ሳይሰስቱ በቅንነትና በታማኝነት ተማሪውን በመቅረፅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አቶ መኮንን አሳስበዋል።
በመርሃ-ግብሩ ማጠቃለያ በ2017 በጀት ዓመት በትምህርት ሥራ ላይ የተሻለ አስተዋፅኦ ላበረከቱ መምህራንና የጽ/ቤቱ ባለሙያዎች የዕውቅናና የሽልማት ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በክራምት ወራት ሲከውኑት የነበረውን የበጎ ተግባር በበጋ ወራት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በስልጤ ዞን የሁልባረግ ወረዳ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተናገሩ
በሀገር በቀል ዕውቀት የሚታወቀውን የአካባቢውን እምቅ አቅም አጉልቶ በማሳየት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ዕድገት ማፋጠን እንደሚገባ ተገለፀ
በሩብ ዓመቱ ከ800 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ