ሃኪም ዚዬች ወደ ዋይዳድ ካዛብላንካ ለመዛወር ተስማማ
የቀድሞ የቼልሲ የፊት መስመር ተጫዋች ሃኪም ዚዬች የሞሮኮውን ክለብ ዋይዳድ ካዛብላንካን ለመቀላቀል ከስምምነት ላይ መድረሱ ተገልጿል።
የ32 ዓመቱ ተጫዋች በነፃ ዝውውር የሀገሩን ክለብ ለመቀላቀል መስማማቱን የፋብሪዚዮ ሮማኖ መረጃ ያስረዳል።
ሃኪም ዚዬች ሦስት የውድድር ዓመታትን በምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ቆይታ ካደረገ በኋላ ወደ ቱርክ አቅንቶ ለጋላታሳራይ መፈረሙ ይታወሳል።
ተጫዋቹ ባለፈው የውድድር ዓመት በኳታሩ ክለብ አል ዱሀይል ተጫውቶ ካሳለፈ በኋላ ውሉ መጠናቀቁን ተከትሎ በሰኔ ወር ቡድኑን ለቆ ያለክለብ ቆይቷል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ምክር ቤቱ በጋሞ ዞን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ3 ሚላዮን ብር ድጋፍ አደረገ
ዲሚትሪ ፓዬት ጫማውን ሰቀለ
የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙ የበና ጸማይ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ