ሃኪም ዚዬች ወደ ዋይዳድ ካዛብላንካ ለመዛወር ተስማማ
የቀድሞ የቼልሲ የፊት መስመር ተጫዋች ሃኪም ዚዬች የሞሮኮውን ክለብ ዋይዳድ ካዛብላንካን ለመቀላቀል ከስምምነት ላይ መድረሱ ተገልጿል።
የ32 ዓመቱ ተጫዋች በነፃ ዝውውር የሀገሩን ክለብ ለመቀላቀል መስማማቱን የፋብሪዚዮ ሮማኖ መረጃ ያስረዳል።
ሃኪም ዚዬች ሦስት የውድድር ዓመታትን በምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ቆይታ ካደረገ በኋላ ወደ ቱርክ አቅንቶ ለጋላታሳራይ መፈረሙ ይታወሳል።
ተጫዋቹ ባለፈው የውድድር ዓመት በኳታሩ ክለብ አል ዱሀይል ተጫውቶ ካሳለፈ በኋላ ውሉ መጠናቀቁን ተከትሎ በሰኔ ወር ቡድኑን ለቆ ያለክለብ ቆይቷል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የፍትህ ዘርፍ ባለሙያዎችን አቅም ማጎልበት በፍትህ ስርዓት ላይ የሚነሱ ችግሮችን እንደሚቀርፍ ተጠቆመ
በስራ ቦታቸው ላይ የህፃናት ማቆያ ማዕከል መቋቋሙ ስራቸውን በአግባቡ ለማከናወን እንዳስቻላቸው የማእከሉ ተጠቃሚ እናቶች ገለፁ
ለግብርናው እድገት መንግስት ከሚያደርገው ጥረት ጎን ለጎን የግብርና አጋር አካላት ድጋፍ የማይተካ ሚና እንዳለው የጎፋ ዞን ግብርና መምሪያ ገለጸ