ሃኪም ዚዬች ወደ ዋይዳድ ካዛብላንካ ለመዛወር ተስማማ
የቀድሞ የቼልሲ የፊት መስመር ተጫዋች ሃኪም ዚዬች የሞሮኮውን ክለብ ዋይዳድ ካዛብላንካን ለመቀላቀል ከስምምነት ላይ መድረሱ ተገልጿል።
የ32 ዓመቱ ተጫዋች በነፃ ዝውውር የሀገሩን ክለብ ለመቀላቀል መስማማቱን የፋብሪዚዮ ሮማኖ መረጃ ያስረዳል።
ሃኪም ዚዬች ሦስት የውድድር ዓመታትን በምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ቆይታ ካደረገ በኋላ ወደ ቱርክ አቅንቶ ለጋላታሳራይ መፈረሙ ይታወሳል።
ተጫዋቹ ባለፈው የውድድር ዓመት በኳታሩ ክለብ አል ዱሀይል ተጫውቶ ካሳለፈ በኋላ ውሉ መጠናቀቁን ተከትሎ በሰኔ ወር ቡድኑን ለቆ ያለክለብ ቆይቷል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የአርሰናል የኋላ ደጀን ቤን ዋይት የውድድር ዓመቱ በጉዳት ተጠናቀቀ
ሰርጂዮ ራሞስ ሲቪያን ለመግዛት ከስምምነት ደረሰ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ