የደቡብ መንገዶች ባለስልጣን ጂንካ ዲስትሪክት በበኩሉ በአከባቢው ያለው የአየር ሁኔትና ናዳ ችግሩን እንዳባባሰው አመላክተዋል ።
አስተያየታቸውን የሰጡን አካላት የመንገዱ መበላሸት ከማህበራዊ ህይወታቸው ባለፈ ለአላስፈላጊ ወጪዎች በመዳረግ በኢኮኖሚያቸውም ላይ ተፅዕኖ በመፍጠሩ መንግስት ለመንገዱ ዘላቂ መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጠይቀዋል፡፡
የወባ ኣሪ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መምህሩ ጌታቸው መንገዱ የኣሪ ዞኑን ከወባ አሪና ሰሜን አሪ ጋር የሚያገናኝ ብቸኛው መንገድ መሆኑን ጠቅሰው፥ በአከባቢው የተከሰተው ናዳ በመንገዱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማስከተሉ ችግሩንም ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር እየተሰራ ነው ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ስራ አስኪያጅ አቶ ሊየው ካሳሁን በበኩላቸው ከማህበረሰቡ የተነሳው ቅሬታ አግባብነት ያለው መሆኑን ጠቁመው፥ በአከባቢው ያለው የዝናብ ሁኔትና ናዳ ችግሩን እንዳባባሰው አድጎታል ብለዋል።
ችግሩንም ለመቅረፍ በቀጣይ ጥናቶች ተደርገው ዘላቂ መፍትሄ እስኪፈጠር ድረስ እንቅስቃሴዎች እንዳይቛረጡ ማሽኖችን በማስገባት ጊዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።
ዘጋቢ፡ በናወርቅ መንግስቱ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በአከባቢዉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር እጥረት ችግር ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው
የአከባቢን እና የሀገርን ሰላም ለማረጋገጥ የሚቻለው ህብረተሰቡን የሰላም ባለቤት ማድረግ ሲቻል መሆኑ ተገለጸ
ምክር ቤቱ በጋሞ ዞን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ3 ሚላዮን ብር ድጋፍ አደረገ