የደቡብ መንገዶች ባለስልጣን ጂንካ ዲስትሪክት በበኩሉ በአከባቢው ያለው የአየር ሁኔትና ናዳ ችግሩን እንዳባባሰው አመላክተዋል ።
አስተያየታቸውን የሰጡን አካላት የመንገዱ መበላሸት ከማህበራዊ ህይወታቸው ባለፈ ለአላስፈላጊ ወጪዎች በመዳረግ በኢኮኖሚያቸውም ላይ ተፅዕኖ በመፍጠሩ መንግስት ለመንገዱ ዘላቂ መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጠይቀዋል፡፡
የወባ ኣሪ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መምህሩ ጌታቸው መንገዱ የኣሪ ዞኑን ከወባ አሪና ሰሜን አሪ ጋር የሚያገናኝ ብቸኛው መንገድ መሆኑን ጠቅሰው፥ በአከባቢው የተከሰተው ናዳ በመንገዱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማስከተሉ ችግሩንም ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር እየተሰራ ነው ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ስራ አስኪያጅ አቶ ሊየው ካሳሁን በበኩላቸው ከማህበረሰቡ የተነሳው ቅሬታ አግባብነት ያለው መሆኑን ጠቁመው፥ በአከባቢው ያለው የዝናብ ሁኔትና ናዳ ችግሩን እንዳባባሰው አድጎታል ብለዋል።
ችግሩንም ለመቅረፍ በቀጣይ ጥናቶች ተደርገው ዘላቂ መፍትሄ እስኪፈጠር ድረስ እንቅስቃሴዎች እንዳይቛረጡ ማሽኖችን በማስገባት ጊዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።
ዘጋቢ፡ በናወርቅ መንግስቱ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ