የደቡብ መንገዶች ባለስልጣን ጂንካ ዲስትሪክት በበኩሉ በአከባቢው ያለው የአየር ሁኔትና ናዳ ችግሩን እንዳባባሰው አመላክተዋል ።
አስተያየታቸውን የሰጡን አካላት የመንገዱ መበላሸት ከማህበራዊ ህይወታቸው ባለፈ ለአላስፈላጊ ወጪዎች በመዳረግ በኢኮኖሚያቸውም ላይ ተፅዕኖ በመፍጠሩ መንግስት ለመንገዱ ዘላቂ መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጠይቀዋል፡፡
የወባ ኣሪ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መምህሩ ጌታቸው መንገዱ የኣሪ ዞኑን ከወባ አሪና ሰሜን አሪ ጋር የሚያገናኝ ብቸኛው መንገድ መሆኑን ጠቅሰው፥ በአከባቢው የተከሰተው ናዳ በመንገዱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማስከተሉ ችግሩንም ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር እየተሰራ ነው ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ስራ አስኪያጅ አቶ ሊየው ካሳሁን በበኩላቸው ከማህበረሰቡ የተነሳው ቅሬታ አግባብነት ያለው መሆኑን ጠቁመው፥ በአከባቢው ያለው የዝናብ ሁኔትና ናዳ ችግሩን እንዳባባሰው አድጎታል ብለዋል።
ችግሩንም ለመቅረፍ በቀጣይ ጥናቶች ተደርገው ዘላቂ መፍትሄ እስኪፈጠር ድረስ እንቅስቃሴዎች እንዳይቛረጡ ማሽኖችን በማስገባት ጊዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት ስራዎች እየተሰሩ ነው ብለዋል።
ዘጋቢ፡ በናወርቅ መንግስቱ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ