ኖቲንግሃም ፎረስት አንጅ ፖስቴኮግሉን አሰናበተ
የእንግሊዙ ክለብ ኖቲንግሃም ፎረስት ዋና አሰልጣኙን አንጅ ፖስቴኮግሉን ከሀላፊነታቸው አሰናብቷቸዋል።
ክለቡ አውስትራሊያዊውን አሰልጣኝ ከሀላፊነታቸው ያሰናበተው ደካማ ውጤት ማስመዝገባቸውን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።
አንጅ ፖስቴኮግሉ ኑኖ ስፕሪቶ ሳንቶን ተከትለው ኖቲንግሃም ፎረስትን መምራት ቢችሉም አንድም ጨዋታ አላሸነፉም።
አሰልጣኝ አንጄ ፖስቴኮግሉ በዚህ ዓመት በፕሪሚየር ሊጉ ከኑኖ ስፕሪቶ ሳንቶ እና ግራሃም ፖተር በመቀጠል 3ኛ ተሰናባች አሰልጣኝ ሆነዋል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሰ

More Stories
አርባምንጭ ከተማ ወደ ታችኛው ሊግ መውረዱ ተረጋገጠ
ዴክላን ራይስ የአርሰናል የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች በመባል ተመረጠ
ፖርቹጋልን ያስደነገጠው ያልተጠበቀው አቻ ውጤት!