ሲዳማ ቡና የውድድር ዓመቱን በድል ጀመረ
በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሲዳማ ቡና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 4ለ1 በማሸነፍ የውድድር ዓመቱን በድል ጀምሯል።
ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሰመረ ሀፍታይ በ36ኛው ደቂቃ ጎል አስቆጥሮ ወልዋሎን መሪ ማድረግ ችሎ ነበር።
ሆኖም ግን በአሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ የሚመራው ሲዳማ ቡና በሁለተኛው አጋማሽ ጌታሁን ባፋ በራሱ ላይ፣ አበባየሁ ሀጂሶ፣ አስቻለው ሙሳ እና ተመስገን መንገሻ ኳስ እና መረብን አገናኝተውለት ጣፋጭ ድል አሳክተዋል።
በ2ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐግር ሲዳማ ቡና ከሀዋሳ ከተማ ጋር ሲጫወት ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከፋሲል ከነማ ጋር የሚገናኝ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ሲዳማ ቡና አቤል ያለውን እና ሱራፌል ዳኛቸውን አስፈረመ
ክርስቲያኖ ሮናልዶ ወደ እግርኳስ ባለቤትነት
አትሌት ቢኒያም መላክ እና ውድነሽ ዓለሙ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የጎዳና ሩጫ ውድድርን አሸነፉ