ሲዳማ ቡና የውድድር ዓመቱን በድል ጀመረ
በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሲዳማ ቡና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 4ለ1 በማሸነፍ የውድድር ዓመቱን በድል ጀምሯል።
ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሰመረ ሀፍታይ በ36ኛው ደቂቃ ጎል አስቆጥሮ ወልዋሎን መሪ ማድረግ ችሎ ነበር።
ሆኖም ግን በአሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ የሚመራው ሲዳማ ቡና በሁለተኛው አጋማሽ ጌታሁን ባፋ በራሱ ላይ፣ አበባየሁ ሀጂሶ፣ አስቻለው ሙሳ እና ተመስገን መንገሻ ኳስ እና መረብን አገናኝተውለት ጣፋጭ ድል አሳክተዋል።
በ2ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐግር ሲዳማ ቡና ከሀዋሳ ከተማ ጋር ሲጫወት ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከፋሲል ከነማ ጋር የሚገናኝ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት