ሞሮኮ አሜሪካን በማሸነፍ ለግማሽ ፍፃሜ ደረሰች
በቺሊ አስተናጋጅነት በመካሄድ ላይ በሚገኘው ከ20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ ሀገር ሞሮኮ አሜሪካን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍፃሜው ደርሳለች።
ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር በሩብ ፍፃሜ ጨዋታ አሜሪካን 3ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ነው ወደ ግማሽ ፍፃሜው የተሻገረችው።
ለአትላስ አንበሳዎቹ ወሳኝ የድል ግቦችን ፉአድ ዛሆኒ፣ ጆሹዋ ዋይንዴር በራሱ ላይ እና ጄሲም ያሲን ከመረብ አሳርፈዋል።
ሞሮኮ በቀጣይ ወደ ፍፃሜ ለማለፍ ከፈረንሳይ ጋር የምትፋለም ይሆናል።
ፈረንሳይ በሩብ ፍፃሜው ኖርዌይን 2ለ1 አሸንፋ ነው ለግማሽ ፍፃሜው የበቃችው።
ሞሮኮ ከፈረንሳይ ጋር የሚያደርጉት ወሳኝ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ የፊታችን ረቡዕ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ይካሄዳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
“አስተናጋጃችን ፊፋ ነው እንጂ ትራምፕ አይደሉም!” – ኢራን
አርሰናል የእንግሊዝ ባለጸጋ ለመሆን ተቃርቧል!
ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠሩ ባሻገር በውሳኔ ሰጪነት ቦታዎች ላይ ኃላፊነት በመስጠት ሀገራዊ ራዕይ እያሳካ እንደሚገኝ በኣሪ ዞን የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ አባላት ገለፁ