ቀይ መስቀል ማህበር በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ሐብት በማሰባሰብና ማህብረሰቡን በማስተባበር እያበረከተ ያለው ሚና ተኪ የለሌው ነው – የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ
ሀዋሳ: መስከረም 27/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ሐብት በማሰባሰብና ማህብረሰቡን በማስተባበር እያበረከተ ያለው አስተዋዕጾ ተኪ የለሌው ነው ሲሉ የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የጂንካ ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኣሪ ዞን የማህብረሰብ አቀፍ የአባላት ምክክር መደረክ አካሂዷል፡፡
በተለያየ ጊዜ በየትኛውም አደጋዎች ቀድሞ በመድረስ ሰብአዊ ድጋፎችን እያደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር፥ በኣሪ ዞን የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ለማድረግ እንደሚሰራ ዋና አስተዳዳሪው ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጂንካ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ቢሻው ጽ/ቤቱ ከተቋቋመ ከ37 ዓመታት በላይ ከብሔራዊ ማህበር ዋና መሥሪያ ቤት ጀምሮ በተዋረድ በጋራ በመቀናጀት የተለያዩ አደጋዎች በሚከሰቱበት ወቅት ፈጣን፣ በጎና ሰብአዊ ድጋፎችን እያደረገ መቆየቱን አብራርተዋል።
ተቋሙ ከዚህ በፊት ከደቡብ ኦሞ ዞን ጋር በጋራ ተዋቅሮ እየሠራ ቆይቶ በቅርብ ጊዜ ቀድሞ የነበረው ዞን በመንግስት መዋቅር ምክንያት ለሁለት በመከፈሉ ተቋሙ በኣሪ ዞን በተደራጀና በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል በሀላፊነት እንደሚሠራ አመላክተዋል፡፡
በዚህም ከራሳቸው ጀምረው አባል በመሆን የዞኑ ህዝብም የቀይ መስቀል አባል ሆኖ በተለያየ መልኩ የሚገለፅ አደጋ ሲከሰት ሰብአዊ አገልግሎቶችን ማግኘት እንዲችሉ በሀላፊነት እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል ።
ተቋሙ ቋሚ የገቢ ምንጭ ኖሮት ራሱን እንዲችል መሥራትን እንደሚጠይቅም ተገልጿል ።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ለኢትዮጵያውያን ዕድል ነው ያሉት በመድረኩ የተገኙት በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የደቡብ ኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ዱንዳ ናቸው።
በሀገሪቱ በሁሉም ቦታ አጋጣሚ በሚከሰቱ አደጋዎች አንዱ ወደ ሌላው በመንቀሳቀስ ሰብአዊ ድጋፎችን የመስጠት ሀላፊነት በመኖሩ የሚደራጁ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችና ማስተባበሪያ ማዕከላት በዚህ ልክ ይሠራሉ ብለዋል።
ዞኑ አዳዲስ አባላትን በማፍራትና ተጨማሪ በጀት መድቦ ማህበሩ በተሻለ መልኩ መሥራት እንዲችል መደገፍ እንደሚያስፈልግ አቶ ተስፋዬ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
በመድረኩ ቀጣይ አባላትን ከማፍራት ጀምሮ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል የውል ስምምነትም ተደርጓል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ