በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር በመንግሥት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ59 ሚሊዮን 7 መቶ ሺህ ብር በላይ ወጪ የተገነቡ ትምህርት ቤቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ
በትምህርት ቤቶቹ መገንባት የአካባቢው ነዋሪና ተማሪዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የጊዞላ መንደር ቅድመ መደበኛ እና 1ኛና መካከለኛ ደረጃ እንዲሁም በልማት ወዜ ቀበሌ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ተመርቀው በይፋ ስራ ጀምረዋል፡፡
የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) የትምህርት ስራ ለሀገር ልማት ወሳኝ በመሆኑ አንደ ከተማ አስተዳደር ተደራሽነቱንና ጥራቱን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የተመረቁት ትምህርት ቤቶች የህዝብ ጥያቄን መሰረት በማድረግ እቅዱን በመንግስትና በህዝብ ተሳትፎ አሳክተን አስመርቀናል ቀሪ ስራዎችንም እንደዚሁ ተቀናጅተን ለማሳካት ጥረት እናደርጋለን ነው ያሉት፡፡
የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ መንዛ፤ ዜጎች በአቅራቢያቸው የመማር እድል እንዲያገኙ ከማድረግ አንፃር የዛሬው ስራ የሚያበረታታ ነው ብለዋል፡፡
በተለይም ይላሉ አቶ መለሰ፤ የጊዞላ አካባቢ ተማሪዎች እስከ ሼቻ እየሄዱ ይንገላቱ የነበሩበትን ችግር እንደሚቀርፍ ተናግረዋል፡፡
በሁለቱም ቀበሌያት የተመረቁ ትምህርት ቤቶች 54 ሚሊዮን 790 ሺህ 325 ብር ወጪ እንደተደረገበትም አክለዋል፡፡
የጊዞላ መንደር ወ/ሮ አስቴር አጪዳና አቶ መስፍን ዳቴ፤ ትምህርት ቤቱ በመገንባቱ የልጆቻቸው ችግር ስለተቀረፈ ደስታቸውን ገልፀዋል፡፡
የልማት ወዜ ቀበሌ ነዋሪ አቶ መለሰ መንጁራ፤ ልጆች መንገድ ሲያቋርጡ በመኪና አደጋ እንዲሁም በጎርፍ ይቸገሩ እንደነበር አውስተው ይህ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በመገንባቱ ደስተኛ ነኝ ይላሉ፡፡
የጊዞላ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና መምህራንም ስሜቶቻቸውን በደስታ ገልፀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ብርሀኑ ዳሾ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር በመንግሥት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ59 ሚሊዮን 7 መቶ ሺህ ብር በላይ ወጪ የተገነቡ ትምህርት ቤቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ