በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር በመንግሥት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ59 ሚሊዮን 7 መቶ ሺህ ብር በላይ ወጪ የተገነቡ ትምህርት ቤቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ
በትምህርት ቤቶቹ መገንባት የአካባቢው ነዋሪና ተማሪዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የጊዞላ መንደር ቅድመ መደበኛ እና 1ኛና መካከለኛ ደረጃ እንዲሁም በልማት ወዜ ቀበሌ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ተመርቀው በይፋ ስራ ጀምረዋል፡፡
የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) የትምህርት ስራ ለሀገር ልማት ወሳኝ በመሆኑ አንደ ከተማ አስተዳደር ተደራሽነቱንና ጥራቱን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የተመረቁት ትምህርት ቤቶች የህዝብ ጥያቄን መሰረት በማድረግ እቅዱን በመንግስትና በህዝብ ተሳትፎ አሳክተን አስመርቀናል ቀሪ ስራዎችንም እንደዚሁ ተቀናጅተን ለማሳካት ጥረት እናደርጋለን ነው ያሉት፡፡
የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ መንዛ፤ ዜጎች በአቅራቢያቸው የመማር እድል እንዲያገኙ ከማድረግ አንፃር የዛሬው ስራ የሚያበረታታ ነው ብለዋል፡፡
በተለይም ይላሉ አቶ መለሰ፤ የጊዞላ አካባቢ ተማሪዎች እስከ ሼቻ እየሄዱ ይንገላቱ የነበሩበትን ችግር እንደሚቀርፍ ተናግረዋል፡፡
በሁለቱም ቀበሌያት የተመረቁ ትምህርት ቤቶች 54 ሚሊዮን 790 ሺህ 325 ብር ወጪ እንደተደረገበትም አክለዋል፡፡
የጊዞላ መንደር ወ/ሮ አስቴር አጪዳና አቶ መስፍን ዳቴ፤ ትምህርት ቤቱ በመገንባቱ የልጆቻቸው ችግር ስለተቀረፈ ደስታቸውን ገልፀዋል፡፡
የልማት ወዜ ቀበሌ ነዋሪ አቶ መለሰ መንጁራ፤ ልጆች መንገድ ሲያቋርጡ በመኪና አደጋ እንዲሁም በጎርፍ ይቸገሩ እንደነበር አውስተው ይህ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤት በመገንባቱ ደስተኛ ነኝ ይላሉ፡፡
የጊዞላ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና መምህራንም ስሜቶቻቸውን በደስታ ገልፀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ብርሀኑ ዳሾ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር በመንግሥት እና በህብረተሰብ ተሳትፎ ከ59 ሚሊዮን 7 መቶ ሺህ ብር በላይ ወጪ የተገነቡ ትምህርት ቤቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ