በሀገር እና ዓለም አቀፍ ደረጃ በጥምርታ ለሚሰሩ የምርምር ሥራዎች እውቅና መስጠት እንደሚገባ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ
የፕሮጀክት እና የህትመት ቀን “የምርምር፣ የፕሮጀክት እና የሕትመት ውስጥ ስኬቶችን ማክበር” በሚል መሪ ሀሳብ በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ እየተከበረ ይገኛል፡፡
በዕለቱ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኢንጂነር አብደላ ከማል እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው የምርምር ዩኒቨርሲቲ እንደመሆኑ መጠን የምርምር ውጤቶችን ሸልፍ ላይ ከማስቀመጥ ባለፈ ለህብረተሰቡ ችግር ፈቺ ሆነው እንዲሰሩ የቀኑ መከበር የሚያነሳሳ ነው።
ዩኒቨርሲቲዎች የሚለኩትና እውቅና የሚያገኙት በሚሰሩት የምርምር ውጤቶች መሆኑን ዶ/ር ኢንጂነር አብደላ ተናግረው፤ በሀገር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በጥምርታ ለሚሰሩ የምርምር ሥራዎች እውቅና መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው በምርምር ሥራ መድረስ ወደሚፈልገው ደረጃ አለመድረሱን ጠቁመው፤ ይህንን ከፍ ለማድረግ የምርምር ሥራዎችን ለሚያከናውኑ መምህራን እውቅና በመስጠት ለማነሳሳት መሆኑን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም ጥናት አቅራቢዎች በፕሮጀክቶች እንዲሳተፉ እናበረታታለን ብለው፤ ከ2018 በጀት ዓመት ጀምሮ የምርምር ውጤቶች ማሳተም ለሁሉም ግዴታ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዕለቱም በፕሮጀትና ህትመት ሥራዎች ዙሪያ ፓናል ውይይት የሚደረግ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት የፕሮጀክት ሥራዎችን ላሸነፉና በርካታ ሥራዎችን ላሳተሙ ተመራማሪዎች እውቅና ይሰጣልቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።
በመርሀ-ግብሩ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኢንጂነር አብደላ ከማልን ጨምሮ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር ተክሉ ወጋየሁ፣ የዩኒቨርሲቲው የምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ተስፋዬ ኃ/ማርያም እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ተመራማራዎች፣ ሴኔት አባላትና መምህራን እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ አስናቀ ካንኮ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
በሀገር እና ዓለም አቀፍ ደረጃ በጥምርታ ለሚሰሩ የምርምር ሥራዎች እውቅና መስጠት እንደሚገባ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ

More Stories
ጃፓን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ብራዚልን አሸነፈች
ከተሞች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው አገልግሎት መሥጠታቸው የተገልጋይና የአገልጋይ ግንኙነት ጤናማና እርካታ የተሞላበት እንዲሆን የሚያስችል መሆኑ ተገለጸ
አቶ ጌታቸው ኬኒ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ሆነው ተሾሙ