በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የመደመር ትዉልድ መጽሐፍ ሽያጭ የጥያ ዓለም አቀፍ መከነ ቅርስ ማልማትና ማስፋፊያ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ የማኖር ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ነዉ
ሀዋሳ፡ መስከረም 24/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የመደመር ትዉልድ መጽሐፍ ሽያጭ የጥያ ዓለም አቀፍ መከነ ቅርስ ማልማትና ማስፋፊያ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ የማኖር ስነ-ስርዓት ዓለም አቀፍ ቅርሱ በሚገኝበት ጥያ እየተካሄደ ነዉ።
በመርሃ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻዉ ጣሰዉ፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋጤ ሰርሞሎ፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር)፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ኤርሲኖ አቡሬ እንዲሁም ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ድልነሳው ታደሰ

More Stories
የደረሱ ሰብሎችን የቤተሰብ ጉልበትና የልማት ቡድን አደረጃጀት በመጠቀም በመሰብሰብ ላይ መሆናቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የባዳ ቀበሌ አርሶ አደሮች ተናገሩ
በመጽናቴ ያገኘሁት ውጤት ነው – አርሶ አደር ደፋር ታደመ
20ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በሰላም መጠናቀቁ ተገለፀ