በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የመደመር ትዉልድ መጽሐፍ ሽያጭ የጥያ ዓለም አቀፍ መከነ ቅርስ ማልማትና ማስፋፊያ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ የማኖር ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ነዉ
ሀዋሳ፡ መስከረም 24/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የመደመር ትዉልድ መጽሐፍ ሽያጭ የጥያ ዓለም አቀፍ መከነ ቅርስ ማልማትና ማስፋፊያ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ የማኖር ስነ-ስርዓት ዓለም አቀፍ ቅርሱ በሚገኝበት ጥያ እየተካሄደ ነዉ።
በመርሃ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻዉ ጣሰዉ፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋጤ ሰርሞሎ፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር)፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ኤርሲኖ አቡሬ እንዲሁም ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ድልነሳው ታደሰ
More Stories
ጃፓን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ብራዚልን አሸነፈች
ከተሞች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዘው አገልግሎት መሥጠታቸው የተገልጋይና የአገልጋይ ግንኙነት ጤናማና እርካታ የተሞላበት እንዲሆን የሚያስችል መሆኑ ተገለጸ
አቶ ጌታቸው ኬኒ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሄረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ሆነው ተሾሙ