በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የመደመር ትዉልድ መጽሐፍ ሽያጭ የጥያ ዓለም አቀፍ መከነ ቅርስ ማልማትና ማስፋፊያ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ የማኖር ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ነዉ
ሀዋሳ፡ መስከረም 24/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የመደመር ትዉልድ መጽሐፍ ሽያጭ የጥያ ዓለም አቀፍ መከነ ቅርስ ማልማትና ማስፋፊያ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ የማኖር ስነ-ስርዓት ዓለም አቀፍ ቅርሱ በሚገኝበት ጥያ እየተካሄደ ነዉ።
በመርሃ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻዉ ጣሰዉ፣ የክልሉ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋጤ ሰርሞሎ፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ(ዶ/ር)፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ኤርሲኖ አቡሬ እንዲሁም ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ድልነሳው ታደሰ

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ