የሙስሊሙ ማህበረሰብ አንድነትና ዘላቂ ሠላምን ለማጠናከር በሚከወኑ ተግባራት ተሳትፏቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ተገለፀ
የጂንካ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ከከተማው ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ጋር በመሆን በ2017 ዓ.ም የመጅሊሱ ምርጫ በሠላምና በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የምስጋናና የዕውቅና ፕሮግራም ተካሂዷል።
የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሲሳይ ጋልሺ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልክት፤ የሙስሊሙ ማህበረሰብ አንድነትና ዘላቂ ሠላምን ለማጠናከር ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነው ይህንን በጎ ተግባር አዲስ ከተመረጡ አመራሮች ጋር በመሆን አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል።
የጂንካ ከተማ ሠላምና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መላኩ አበራ እና የከተማው ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ካሌብ ከብትመር፤ የመጅሊስ ምርጫው በሠላም እንዲጠናቀቅ በትኩረት መሠራቱን አንስተው የሙስሊሙ ማህበረሰብ ሠላምና አንድነትን በማጠናከር ከመንግስት ጎን በመሆን ለጋራ ልማትና ብልፅግና የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
የኣሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ጀማል ሙሀመድ እና የጂንካ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ኃላፊ አቶ ኡሚሬድን ግርማ የመድረኩን ዓላማ ገልፀው ሁለንተናዊ ዕድገትና ዘላቂ ሠላምን ለማስፈን አዲስ ከተመረጡ አባላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠሩም ገልፀዋል።
በቀጣይ አምስት አመታት በልማት፣ በሠላምና አንድነትን ይበልጥ የሚያጠናክሩ ተግባራትን በማከናወን የተጣለባቸውን ኃላፊነት በታማኝነትና በአግባቡ ለመወጣት መዘጋጀታቸውን አዲስ የተመረጡ አባላት ተናግረዋል።
የጂንካ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ከከተማው ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ጋር በመሆን በ2017 ዓ.ም የመጅሊሱ ምርጫ በሠላምና በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትና ከዚህ በፊት ላገለገሉ አመራሮች የምስጋናና የዕውቅና ሽልማት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ማሳቸውን ለመኸር እርሻ ደጋግማው በማረስ አለስልሰው በወቅቱ ለመዝራት መዘጋጀታቸውን በከምባታ ዞን ቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ያነጋገርናቸው አንዳንድ አርሶአደሮች ተናገሩ
በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ የስራ ዘርፎች ከ40 ሺህ በላይ ወጣቶችን ተሳታፊ በማድረግ 46 ሚሊዮን 620 ሺህ ብር በላይ ከመንግሥት ሊወጣ የሚችለውን ለማዳን ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አስታወቀ
የቀቤና ልዩ ወረዳ ማህበረሰብ የልማት ፍላጎት ማሟላት የሚቻለው ግብርና ታክስ በታማኝነትና በወቅቱ መክፈል ሲቻል መሆኑ ተገለጸ