“ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ ነው” – በቦንጋ ከተማ የድጋፍ ሰልፍ ተሳታፊዎች
“ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ ነው” ሲሉ በቦንጋ ከተማ የድጋፍ ሰልፍ ተሳታፊዎች ገልጸዋል፡፡
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን አስመልክቶ በቦንጋ ከተማ ክልላዊ የማጠቃለያ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል፡፡
በሰልፉ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የፀጥታ አካላትን አነጋግረናል፡፡
ህዳሴ ግድቡ ለኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ ነው ሲሉ ሃሳባቸውን ሰጥተዋል፡፡
የግድቡ መጠናቀቅ የዘመናት ቁጭታችን መቋጫና የኢትዮጵያዊነት ማረጋገጫ ነው ብለዋል፡፡
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ከድህነት የምትወጣበትና በጨለማ ውስጥ ለነበሩ ህዝቦች ብርሀን የሚሆን ነው ብለዋል፡፡
ከ14 ዓመታት የግንባታ ጊዜ ቆይታ በኋላ ግድቡ በመጠናቀቁ መደሰታቸውን አስተያየት ተሰጪዎቹ ገልጸዋል፡፡
ግድቡ የእንችላለን መንፈስን በተግባር ያስመሰከረና ሌሎች ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን አቅም የፈጠረ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
ምክር ቤቱ በጋሞ ዞን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ3 ሚላዮን ብር ድጋፍ አደረገ
የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙ የበና ጸማይ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በክልሉ ከቱሪዝሙ ዘርፍ ባለፉት 9 ወራት 925.6 ሚሊዮን ብር ተገኝቷል