“ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ ነው” – በቦንጋ ከተማ የድጋፍ ሰልፍ ተሳታፊዎች
“ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ ነው” ሲሉ በቦንጋ ከተማ የድጋፍ ሰልፍ ተሳታፊዎች ገልጸዋል፡፡
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን አስመልክቶ በቦንጋ ከተማ ክልላዊ የማጠቃለያ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል፡፡
በሰልፉ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የፀጥታ አካላትን አነጋግረናል፡፡
ህዳሴ ግድቡ ለኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ ነው ሲሉ ሃሳባቸውን ሰጥተዋል፡፡
የግድቡ መጠናቀቅ የዘመናት ቁጭታችን መቋጫና የኢትዮጵያዊነት ማረጋገጫ ነው ብለዋል፡፡
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ ከድህነት የምትወጣበትና በጨለማ ውስጥ ለነበሩ ህዝቦች ብርሀን የሚሆን ነው ብለዋል፡፡
ከ14 ዓመታት የግንባታ ጊዜ ቆይታ በኋላ ግድቡ በመጠናቀቁ መደሰታቸውን አስተያየት ተሰጪዎቹ ገልጸዋል፡፡
ግድቡ የእንችላለን መንፈስን በተግባር ያስመሰከረና ሌሎች ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን አቅም የፈጠረ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ