“ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ምልክት ነው” – ሰልፈኞች
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅን አስመልክቶ በቦንጋ ከተማ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው፡፡
ያነጋገርናቸው የሰልፉ ተሳታፊዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ ለምረቃ በመብቃቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡
ለግድቡ ግንባታ ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውሰው፤ ግድቡ ለኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ምልክት ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ ያለው ትርጉምና አንደምታ ልዩ ነው ሲሉም ነው የገለጹት፡፡
በድጋፍ ሰልፉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የስድስቱም ዞኖች አስተዳዳሪዎች፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ