“ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ምልክት ነው” – ሰልፈኞች
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅን አስመልክቶ በቦንጋ ከተማ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው፡፡
ያነጋገርናቸው የሰልፉ ተሳታፊዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ ለምረቃ በመብቃቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡
ለግድቡ ግንባታ ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውሰው፤ ግድቡ ለኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ምልክት ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ ያለው ትርጉምና አንደምታ ልዩ ነው ሲሉም ነው የገለጹት፡፡
በድጋፍ ሰልፉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የስድስቱም ዞኖች አስተዳዳሪዎች፣ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ