ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቦንጋ ከተማ የድጋፍና የደስታ መግለጫ ሰልፍ እየተካሄደ ነው
የግድቡ ግንባታ በድል እንዲጠናቀቅ መንግስት የወሰደውን አቋም የሚደግፉ መፈክሮችን የያዙ ሰልፈኞች ከተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ቦንጋ ከተማ ገብተዋል።
“በኅብረት ችለናል” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ባለው የድጋፍና ደስታ መግለጫ በሆነው በዚህ ሰልፍ ላይ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያንን የዘመናት ቁጭት የመለሰ ነው፣ ሕዳሴ ግድብ የአንድነትና የጽናት ውጤት ማሳያ ነው፣ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጅማሮ ምልክት ነው፣ ህዳሴ ግድብ የከበረ በላብ የታሰረ፣ ግድባችን የህብረ ብሔራዊነታችን እና የአንድነታችን መሰረት የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን ሰልፈኞቹ በአደባባይ እያሰሙ ነው።
የድጋፍ ሰልፉ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ሲደረግ ቆይቶ ዛሬ ክልላዊ ማጠቃለያው በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡
ዘጋቢ፡ አሳምነው አትርሳው – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ