ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቦንጋ ከተማ የድጋፍና የደስታ መግለጫ ሰልፍ እየተካሄደ ነው
የግድቡ ግንባታ በድል እንዲጠናቀቅ መንግስት የወሰደውን አቋም የሚደግፉ መፈክሮችን የያዙ ሰልፈኞች ከተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ቦንጋ ከተማ ገብተዋል።
“በኅብረት ችለናል” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ባለው የድጋፍና ደስታ መግለጫ በሆነው በዚህ ሰልፍ ላይ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያንን የዘመናት ቁጭት የመለሰ ነው፣ ሕዳሴ ግድብ የአንድነትና የጽናት ውጤት ማሳያ ነው፣ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጅማሮ ምልክት ነው፣ ህዳሴ ግድብ የከበረ በላብ የታሰረ፣ ግድባችን የህብረ ብሔራዊነታችን እና የአንድነታችን መሰረት የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን ሰልፈኞቹ በአደባባይ እያሰሙ ነው።
የድጋፍ ሰልፉ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ሲደረግ ቆይቶ ዛሬ ክልላዊ ማጠቃለያው በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡
ዘጋቢ፡ አሳምነው አትርሳው – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
ምክር ቤቱ በጋሞ ዞን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ3 ሚላዮን ብር ድጋፍ አደረገ
የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙ የበና ጸማይ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በክልሉ ከቱሪዝሙ ዘርፍ ባለፉት 9 ወራት 925.6 ሚሊዮን ብር ተገኝቷል