ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቦንጋ ከተማ የድጋፍና የደስታ መግለጫ ሰልፍ እየተካሄደ ነው
የግድቡ ግንባታ በድል እንዲጠናቀቅ መንግስት የወሰደውን አቋም የሚደግፉ መፈክሮችን የያዙ ሰልፈኞች ከተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ቦንጋ ከተማ ገብተዋል።
“በኅብረት ችለናል” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ባለው የድጋፍና ደስታ መግለጫ በሆነው በዚህ ሰልፍ ላይ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያንን የዘመናት ቁጭት የመለሰ ነው፣ ሕዳሴ ግድብ የአንድነትና የጽናት ውጤት ማሳያ ነው፣ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጅማሮ ምልክት ነው፣ ህዳሴ ግድብ የከበረ በላብ የታሰረ፣ ግድባችን የህብረ ብሔራዊነታችን እና የአንድነታችን መሰረት የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን ሰልፈኞቹ በአደባባይ እያሰሙ ነው።
የድጋፍ ሰልፉ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ሲደረግ ቆይቶ ዛሬ ክልላዊ ማጠቃለያው በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡
ዘጋቢ፡ አሳምነው አትርሳው – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ