በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ አስተዳደር ሁለት ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ ዘመናዊ ሆቴሎችን ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ
ዓለም አቀፍ ሆቴሎቹ አብዮት አገዘ እና ጴጥሮስ ጀጎ በተባሉ የግል ባላሃብቶች የሚገነቡ መሆናቸውም በዚህ ወቅት ተመላክቷል።
የግንባታ የመሠረት ድንጋዩን የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ እና የዲላ ከተማ የሥራ ኃላፊዎች በጋራ ያስቀመጡ ሲሆን የሆቴሎቹ መገንባት በከተማው የሆቴል ኢንዱስትሪውን የሚያሳድግ መሆኑም ተጠቁሟል።
ሆቴሎቹ ተገንብተው ሲጠናቀቁ ዓለም አቀፍ የጥራት መለኪያዎችን በሟሟላት አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩም ተነግሯል።
ይኸውም በሆቴል ቱሪዝም ዘርፍ የታቀደውን ዕቅድ በማሳካት የከተማውን ዕድገትና ልማት ለማፋጠን ብሎም ተወዳዳሪነቱን የሚያረጋግጥ መሆኑንም ነው ዶክተር ዝናቡ ወልዴ ያብራሩት።
ሆቴሎቹን በአጭርና በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ ዞኑና ከተማ አስተዳደሩ በጋራ በመቀናጀት ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉም ተገልጿል።
የዲላ ከተማን ሞዴልና ተመራጭ ማዕከል ከማድረግም በላይ ለነዋሪዎቿ ምቹ የመኖሪያ ሥነምሕዳር ለመፍጠር ሌሎች በኢንቨስትመንት ዘርፍ የሚሰማሩ የግል ባለሀብቶችን ለመጋበዝ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች በመሠራት ላይ እንደሚያገኙም ተብራርቷል።
ዘጋቢ:- እስራኤል ብርሃኑ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ