በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ አስተዳደር ሁለት ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ ዘመናዊ ሆቴሎችን ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ
ዓለም አቀፍ ሆቴሎቹ አብዮት አገዘ እና ጴጥሮስ ጀጎ በተባሉ የግል ባላሃብቶች የሚገነቡ መሆናቸውም በዚህ ወቅት ተመላክቷል።
የግንባታ የመሠረት ድንጋዩን የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ እና የዲላ ከተማ የሥራ ኃላፊዎች በጋራ ያስቀመጡ ሲሆን የሆቴሎቹ መገንባት በከተማው የሆቴል ኢንዱስትሪውን የሚያሳድግ መሆኑም ተጠቁሟል።
ሆቴሎቹ ተገንብተው ሲጠናቀቁ ዓለም አቀፍ የጥራት መለኪያዎችን በሟሟላት አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩም ተነግሯል።
ይኸውም በሆቴል ቱሪዝም ዘርፍ የታቀደውን ዕቅድ በማሳካት የከተማውን ዕድገትና ልማት ለማፋጠን ብሎም ተወዳዳሪነቱን የሚያረጋግጥ መሆኑንም ነው ዶክተር ዝናቡ ወልዴ ያብራሩት።
ሆቴሎቹን በአጭርና በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ ዞኑና ከተማ አስተዳደሩ በጋራ በመቀናጀት ተገቢውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉም ተገልጿል።
የዲላ ከተማን ሞዴልና ተመራጭ ማዕከል ከማድረግም በላይ ለነዋሪዎቿ ምቹ የመኖሪያ ሥነምሕዳር ለመፍጠር ሌሎች በኢንቨስትመንት ዘርፍ የሚሰማሩ የግል ባለሀብቶችን ለመጋበዝ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች በመሠራት ላይ እንደሚያገኙም ተብራርቷል።
ዘጋቢ:- እስራኤል ብርሃኑ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ