በጎፋ ዞን 5ኛ ዩኒየን የሆነዉ የቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ዩኒየን መሰራች ኮሚቴ መድረክ በሳዉላ ከተማ ተካሄደ
የህብረት ሥራ ማህበራት ማህበራዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን የጎፋ ዞን ህብረት ሥራ ጽ/ቤት ገልጿል።
የቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ዩኒየን መስራች ኮሚቴ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጎፋ ዞን ህብረት ሥራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብረሃኑ ደቻሳ፤ በዞኑ ካለዉ ህዝብ ቁጥር አንፃር በህብረት ሥራ ማህበር ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱት ከ16 ሺህ የማይበልጥ ህዝብ መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም በዞኑ ከ150 የማይበልጡ ህብረት ሥራ ማህበራት መኖራቸዉን አሰታዉሰዉ፤ የዞኑን ህዝብ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታ አዲስ ህብረት ሥራ ማህበራትንና ዩኒየኖችን መፍጠር እንዳለባቸው ገልፀዋል።
የኑሮ ዉድነቱን በማረጋጋት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ በህብረት ሥራ ማህበራት ተደራጅቶ መንቀሳቀስ አማራጭ የሌለዉ ጉዳይ መሆኑን አቶ ብረሃኑ አሳስበዋል።
አሁን እየተደራጀ ያለዉ የቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ዩኒየን የአባላቱን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ከማሳደግ ባለፈ በሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የራሱን አሻራ ለማኖር ውጤታማ ስልት ቀይሶ እንዲሰራ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የህብረት ሥራ ማህበራት አደረጃጀት መመሪያ ቁጥር 896/2014 ዙሪያ ለመስራች ኮሚቴዎች ማብራሪያ የሰጡት የዞኑ ህብረት ሥራ ጽ/ቤት የህብረት ሥራ ማህበራት ማደራጃና ማስፋፊያ ቡድን መሪ አቶ ወንዱ ደበበ፤ የቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ዩኒየኑ በዉስጡ 27 ማህበራትን ያቀፈ ሲሆን ለበለጠ ዉጤታማነት ይሰራል ብለዋል።
የመሰራች ዩኒየን አባል ከሆኑ ማህበራት የዛሎ ማሶና የሳዉላ ከተማ መምህራና ሠራተኞች ገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ሥራ ማህራት በአብነት ተጠቅሰዋል።
የዩኒየኑን ስያሜ፣ መተዳደሪያ ዉስጠ ደንብና ተያያዥ ጉዳዮችን የሚያዘጋጁ አምስት የመስራች ኮሚቴ አባላት ምርጫ በማድረግ መድረኩ ተጠናቋል።
ዘጋቢ፡ መንግስቱ ታሪኩ – ከሳዉላ ጣቢያችን
More Stories
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ በራስ አቅም ጀምራ መጨረስን ያሳየችበት ዳግማዊ የአድዋ ድል የሆነ እና የወል ትርክትን ያፀና ፕሮጀክት መሆኑን የእኖር ወረዳ አስተዳደር ገለጸ
በጋሞ ዞን ውስጥ ያሉ የሶስቱን ነባር ብሔረሰቦች ዘመን መለወጫ በዓላቸውን ጨምሮ ቋንቋን፣ ታሪክንና ባህላዊ ዕሴቶችን በጥናትና ምርምር በማጉላት ለተጠቃሚነት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ ተገለፀ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ አስተዳደር ሁለት ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቁ ዘመናዊ ሆቴሎችን ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ