የካፈቾ ዘመን መለወጫ “ማሽቃሮ” በቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተከበረ
የኮሌጁ ዲን ኢንስትራክተር አንዱዓለም ገብረመድህን ማሽቃሮ ከምክረቾ ስርዓት ጀምሮ ከማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ጋር ተያይዞ ሲከበር የቆየ ነው ብለዋል።
በዓሉ ከክረምት አዝመራ 77 ቀናት መጠናቀቅ ጋር ተያይዞ በወቅቱ በተደረጉ የግብርና እንቅስቃሴዎች የተመዘገቡ ወጤቶች ተገምግመው የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ እውቅና የሚሰጣቸው እንዲሁም ድክመት ያሳዩ በጠንካሮች የሚተኩበት ስርዓት እንደነበር ተናግረዋል።
ይህ ስርዓት በአካባቢው የተሻለ ተግባር እንዲኖር የሚያበረታታ መሆኑን ጠቁመው፥ ይህንን ተሞክሮ ወደ ተቋማት እንዲሸጋገር ማድረግ ይገባል ብለዋል።
በዓሉ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተጠናቀቀበትና የካፋ ነገስታት ዘውድና መቀመጫ ከረጅም ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደቀድሞ ቦታው በተመለሰበት ወቅት የሚከበር መሆኑ እጅግ የተለየ ያደርገዋል ብለዋል።
ከበዓሉ ታዳሚዎች መካከል አቶ ንጋቱ ዓለሙ፣ ኢንስትራክተር አስቻለው ገብረሚካኤል፣ አቶ ፍቃዱ ኃይሌ እና አቶ አስማማው ገዛኸኝ ማሽቃሮ የካፈቾ ብሔረሰብ የራሱ መገለጫ እንዳለው ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል።
በተለይም የካፋ የመጨረሻው ንጉስ ጋኪ ሻሮቺ ዘውድና መቀመጫቸው በተመለሰበት ወቅት በዓሉን በማክበራቸው መደሰታቸውን ጠቁመዋል።
በመጪዉ መስከረም 12 እና 13 ቀን 2018 ዓመተ-ምህረት በቦንጌ ሻምበቶ የሚከበረውን የብሔሩን ዘመን መለወጫ በድምቀት ለማክበር ዝግጅት እያደረጉ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ አሰግድ ሣህሌ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ