በመድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳኜ ህዶ፤ ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ ከውስጥም ከውጭም እየተነሱ የነበሩ ተግዳሮቶችን ተጋፍጣ ግንባታውን በማጠናቀቋ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
እንደ ኢትዮጵያ ብዙ ፕሮጀክቶችን አሳክተናል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ በዞኑ እየመጡ ያሉ ለውጦች ቢኖሩም ገና ብዙ የሚቀር በመሆኑ ሁሉም የዞኑ ነዋሪዎች እጅ ለእጅ ተያይዘዉ እንዲሠሩም አሳስበዋል።
የቡርጂ ዞን ብልጽግና ፓርት ቅንርጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ኡሜ ቾኮል በበኩላቸው፤ የህዳሴ ግድብ በብዙ ተፅዕኖ አልፎ ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ ባደረገው ርብርብ የተጠናቀቀ ፕሮጀክት በመሆኑ ልንኮራ ይገባል ብለዋል።
አክለውም በህብረት ከተሰለፍን የትኛውንም ተግባር በራሳችን አቅም መሥራት እንደምንችል ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
በመረድኩ በቀረበው መነሻ ጽሑፍ ላይ የአባይ ወንዝ ታሪካዊ ዳራ፣ በህዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደት የነበሩ ልዩ ልዩ ተግዳሮቶች እና የህዳሴ ግድብ አንደምታዎች ላይ ገለፃ ተደርጎ ውይይት ተደርጓበታል።
የመድረኩ ተሳታፊዎችም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከዘመናት ቁጭት የወጣንበት፣ የአላማ ፅናት ያሳየንበት እና በህብረት መቻላችንን ያረጋገጥንበት የዚህ ትውልድ አድዋ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዞኑ ህዝብም ከዚህ ትምህርት በመውሰድ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለድል ማብቃት እንዳለበትና በትምህርት ጥራት ላይም መድገም እንደሚያስፈልግ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ዘጋቢ: ቦጋለ ሉሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚወጡ ተመራቂ ሰልጣኞች በሰለጠኑበት ዘርፍ ሀገሪቱ ለጀመረችው የብልጽግና ጉዞ የድርሻቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ
ለትውልድ ግንባታ መሠረት ለሆነው የሞዴል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ትኩረት ተሰጥቶ ሊሠራ ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ምሁር-አክሊል ወረዳ በመንግስትና በህብረተሰቡ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ነው