በመድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳኜ ህዶ፤ ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ ከውስጥም ከውጭም እየተነሱ የነበሩ ተግዳሮቶችን ተጋፍጣ ግንባታውን በማጠናቀቋ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
እንደ ኢትዮጵያ ብዙ ፕሮጀክቶችን አሳክተናል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ በዞኑ እየመጡ ያሉ ለውጦች ቢኖሩም ገና ብዙ የሚቀር በመሆኑ ሁሉም የዞኑ ነዋሪዎች እጅ ለእጅ ተያይዘዉ እንዲሠሩም አሳስበዋል።
የቡርጂ ዞን ብልጽግና ፓርት ቅንርጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ኡሜ ቾኮል በበኩላቸው፤ የህዳሴ ግድብ በብዙ ተፅዕኖ አልፎ ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ ባደረገው ርብርብ የተጠናቀቀ ፕሮጀክት በመሆኑ ልንኮራ ይገባል ብለዋል።
አክለውም በህብረት ከተሰለፍን የትኛውንም ተግባር በራሳችን አቅም መሥራት እንደምንችል ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
በመረድኩ በቀረበው መነሻ ጽሑፍ ላይ የአባይ ወንዝ ታሪካዊ ዳራ፣ በህዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደት የነበሩ ልዩ ልዩ ተግዳሮቶች እና የህዳሴ ግድብ አንደምታዎች ላይ ገለፃ ተደርጎ ውይይት ተደርጓበታል።
የመድረኩ ተሳታፊዎችም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከዘመናት ቁጭት የወጣንበት፣ የአላማ ፅናት ያሳየንበት እና በህብረት መቻላችንን ያረጋገጥንበት የዚህ ትውልድ አድዋ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዞኑ ህዝብም ከዚህ ትምህርት በመውሰድ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በጋራ ለድል ማብቃት እንዳለበትና በትምህርት ጥራት ላይም መድገም እንደሚያስፈልግ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ዘጋቢ: ቦጋለ ሉሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ