በጎፋ ዞን “ከግድቡ ወደ ወደብ ” በሚል መሪ ቃል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን በማስመልከት የፓናል ዉይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ ላይ በሳወላ ከተማ ከሚገኙ የክልል ተቋማት፣ የሳውላ ከተማ አስተዳደር፣ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች እና ባለሙያዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተሳትፈዋል፡፡
የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ፤ የህዳሴውን ግድብ እኛ ኢትዮጵያዊያን በራሳችን አቅም በመገንባታችን ከእኛ አልፎ ለአፍሪካዊያን የኩራት ምንጭና ከአይችሉም መንፈስ ወጥተን መቻላችንን ያረጋገጥንበት የትውልድ አሻራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያን ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ መነሻ በማድረግ የዜጎችን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አኳያ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸው፤ ባለፉት ጊዜያት ሀገር የመሩ መንግስታት የሞከሩት በአሁኑ መቻላችን ትልቅ አቅም መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ምክትልና የወንጀልና የፍትሐብሔር ዘርፍ ኃላፊ አቶ አድማሱ መንግሥቱ ተናግረዋል፡፡
በዚህም ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የህዳሴው ግድብ ዋነኛው ሲሆን ኢትዮጵያ የተከፈተባትን ሁሉን አቀፍ ጦርነትና ዘመቻ ተቋቁማ ታላላቅ ድሎችን ማስመዝገብ እንደምትችል ያስመሰከረችበት ነው ብለዋል።
የሣውላ ከተማ ከንቲባ ዶክተር ንጉሴ መኮንን በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ የዓለም የጥቁር ህዝቦች የእኩልነት መገለጫ፣ የአፍሪካ ተምሳሌትና የአይበገሬነት ማሳያ መሆኗን ጠቅሰው ግድቡ ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ባሻገር የቅኝ ግዛት ትርክትን የሰበረ የዚህ ትውልድ ዳግማዊ አድዋ ነው።
የውይይቱ ተሳታፊዎች የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያውያን አልፎ ለመላው አፍሪካውያን የይቻላል ምልክት ማሳያ አርማ የሆነበት ፤ ወደ ባህር በር ሥራ የምንሰማራበት ነው ብለዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ስንታየሁ ሙላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ