ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን ተከትሎ “በህብረት ችለናል” በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት መድረክ በጂንካ ከተማ ተካሄደ
ሀዋሳ፡ መስከረም 07/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን ተከትሎ “በህብረት ችለናል” በሚል መሪ ቃል የኣሪ ዞን አስተዳደር የጂንካ ክላስተር ክልል ተቋማት በጋራ ያዘጋጁት የፓናል ውይይት መድረክ በጂንካ ከተማ እየተካሄደ ነው።
ፈተናዎችን በብልጠት በመሻገር ለስኬት በቅተናል ሲሉ መድረኩን በንግግር የከፈተቱት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ ገልፀዋል።
የዛሬው ትውልድ ነገ የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ጠንክሮ መሥራት አለበት ሲሉም ወ/ሮ ፀሐይ አሳስበዋል።
የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ በበኩላቸው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የብሔራዊ ኩራታችን አርማ፣ በአለም አደባባይ ጀምረን መጨረስ እንደሚንችል ተምሳሌታችን ነው ብለዋል።
በቀጣይ ግዙፍ የልማት ውጥኖችን ለማሳካት ከህዳሴ ግድብ ትልቅ ትምህርት የተወሰደበትም ነው ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው ገልፀዋል።
ግድቡ በድል ተጠናቅቆ በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ በመግባቱ እንኳን ደስ አለን መልዕክትም አስተላልፈዋል ።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ