ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን ተከትሎ “በህብረት ችለናል” በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት መድረክ በጂንካ ከተማ ተካሄደ
ሀዋሳ፡ መስከረም 07/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን ተከትሎ “በህብረት ችለናል” በሚል መሪ ቃል የኣሪ ዞን አስተዳደር የጂንካ ክላስተር ክልል ተቋማት በጋራ ያዘጋጁት የፓናል ውይይት መድረክ በጂንካ ከተማ እየተካሄደ ነው።
ፈተናዎችን በብልጠት በመሻገር ለስኬት በቅተናል ሲሉ መድረኩን በንግግር የከፈተቱት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ ገልፀዋል።
የዛሬው ትውልድ ነገ የተሻለች ኢትዮጵያን ለማስረከብ ጠንክሮ መሥራት አለበት ሲሉም ወ/ሮ ፀሐይ አሳስበዋል።
የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ በበኩላቸው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የብሔራዊ ኩራታችን አርማ፣ በአለም አደባባይ ጀምረን መጨረስ እንደሚንችል ተምሳሌታችን ነው ብለዋል።
በቀጣይ ግዙፍ የልማት ውጥኖችን ለማሳካት ከህዳሴ ግድብ ትልቅ ትምህርት የተወሰደበትም ነው ሲሉ ዋና አስተዳዳሪው ገልፀዋል።
ግድቡ በድል ተጠናቅቆ በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ በመግባቱ እንኳን ደስ አለን መልዕክትም አስተላልፈዋል ።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ