አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኖ ወደ ቤኔፊካ
ከቀናት በፊት ከቱርኩ ክለብ ፌኔርባቼ አሰልጣኝነት የተሰናበቱት ጆዜ ሞሪኖ ቤኔፊካን በዋና አሰልጣኝነት ለመረከብ ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።
የፖርቹጋሉ ክለብ ቤኔፊካ ትናንት ምሸት በሻምፒዮንስ ሊጉ ከ2ለ0 መምራት ተነስቶ 3ለ2 ከተሸነፈ በኋላ አሰልጣኝ ብሩኖ ላዥን ከሃላፊነታቸው አሰናብቷል።
በዚህ መነሻ ቤኔፊካ ከ19 ቀናት በፊት ከሀላፊነት የተነሱትን አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኖን ለመሾም ተስማምቷል።
በአውሮፓ በርካታ ክለቦችን ማሰልጠን ያቻሉት ሞሪኖ ከ21 ዓመታት በኋላ ወደ ሀገራቸው ሊግ የሚመለሱ ይሆናል።
ጆዜ ሞሪኖ ቤኔፊካን የሚይዙ ከሆነ ከ13 ቀናት በኋላ የቀድሞ ክለባቸው ቼልሲን በሻምፒዮንስ ሊጉ ይገጥማሉ።
ዘጋቢ: ሙሉቀን ባሳ
More Stories
የሴቶች የ3 ሺ ሜትር መሰናክል ፍፃሜ በዛሬዉ ዕለት ይካሄዳል
ሪያል ማድሪድ እና ቶትንሃም ተጋጣሚዎቻቸውን ሲያሸንፉ ዩቬንቱስ እና ዶርትሙንድ አቻ ተለያይተዋል
አትሌት ፍሬወይኒ ሃይሉ በሜዳልያ ሰንጠረዥ ውስጥ መግባት አልቻለችም