ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የህብረ ብሄራዊነታችንና የአንድነታች መገለጫ ከመሆኑም በላይ በላብና ደም የተገኘ ውጤት መሆኑ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ መስከረም 07/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን የህብረ ብሄራዊነታችንና አንድነታችን መገለጫ ከመሆኑም በላይ በላብና በደም የተገኘ ውጤት ነው ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ል ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ አቶ ማሄ ቦዳ ገለጹ፡፡
በከፍተኛ የሀገር ፍቅር ስሜት ገንብተን ዘመን ተሻጋሪ የትውልድ አሻራ በማኖራችን ለመላው ኢትዮጵውያን ምስጋና ይገባል ተብሏል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ “በህብረት ችለናል”በሚል መሪ ቃል በአርባምንጭ ከተማ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ የአርባምንጭ ከተማ ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) እንዳሉት የኢትዮጵያ ኩራት፣ የአንድነታችን ማሳያ፣ የወል ስኬታችን የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በከፍተኛ መስዋእትነት መጠናቀቁን አንስተዋል።
በአድዋ የተገኘውን ታላቅ ድል አባቶቻችን ለኛ እንዳስረከቡን ሁሉ እኛም ለመጭው ትውልድ የሚተርፍና ብርሀን የሚሆን የታላቁን የህዳሴ ግድብ ተክለን ማቆም መቻላችን ትልቅ ኩራት ነው ብለዋል።
ለግድቡ ግንባታ ዝቅተኛ ገቢ ካለው እስከ ታዳጊ ተማሪ ድረስ በከፍተኛ የሀገር ፍቅር ስሜት ገንብተን ይህን ዘመን ተሻጋሪ የትውልድ አሻራ በማኖራችን ለመላው ኢትዮጵውያን ምስጋና ይገባናል ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጽያ ክልል ም/ል ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ አቶ ማሄ ቦዳ አባይ ለዘመናት አፈራችንን እየሸረሸረ ለሌሎች ሀገራት ሲሳይ ሲሆን ከቆየበት አሁን ማደርያውን አግኝቶ እጅ መስጠቱ በይቻላል መንፈስና ብርቱ ጥረት በመገንባቱ ነው ብለዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከሀይል ምንጭነት ባሻገር በራስ አቅም መስራትን፣ ጫና መቋቋምን ያስተማረን፣ ከአይችሉም መንፈስ ወደ ይቻላል እንድንሸጋገር ያደረገ ድላችን መሆኑን ጠቅሰዋል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የህብረ ብሄራዊነታችንና የአንድነታች መገለጫ ከመሆኑም በላይ በላብና ደም የተገኘ ውጤት ነው ፤ በቀጣይ መሠል ፕሮጀክቶችን ለመገንባት በር የሚከፍት እንደሆነም ተናግረዋል።
በፓናል ውይይቱ ላይ ከአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከዞንና ከክልል ተቋማት የተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች ፣ ባለሙያዎችና ምሁራን እየተሳተፉበት ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ማርታ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ