ሙያዊ ስነ-ምግባር የተላበሰ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
ሀዋሳ፡ መስከረም 06/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሙያዊ ስነ-ምግባር የተላበሰ አገልግሎት በመስጠት በፍትህ ዘርፍ የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ገለጸ፡፡
የጉራጌ ዞን ፍትህና ፖሊስ መምሪያ በታክቲክና ቴክኒክ ወንጀል ምርመራ ዙሪያ ለስር መዋቅር ፖሊስና ዐቃቢያነ ህግ ከመስከረም 6-7/2018 ዓ.ም ግንዛቤ ለመስጠት የተዘጋጀ የስልጠና መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኤልያስ ሰብለጋ በመክፈቻ ንግግራቸው ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመጠቀም በርካታ ወንጀሎች የሚፈፀሙ በመሆኑ ይሔንን ለመግታት የፖሊስና የዐቃቢያነ ህግ ክህሎትና አቅም ማሳደግ ይገባል ብለዋል።
በየቦታው የተለያየ መጠን ያላቸው የትራፊክ አደጋዎች እንደሚከሰቱ የገለፁት ሃላፊው ይህንን አደጋ በሳይንሳዊ መንገድ ምርመራ በማድረግ ለውሳኔ ማቅረብ እንደሚገባ ተናግረዋል።
የቴክኒክና የታክቲክ ምርመራ ከጊዜው ጋር አብሮ በሚሔድ መልኩ ስልጠና መስጠት በፍትህ ዘርፍ ላይ አይነተኛ ለውጥ ያመጣል ሲሉ አቶ ኤልያስ ተናግረዋል።
አክለውም የሚፈለገውን አገልግሎት መስጠት እንዲቻል ለህብረተሰቡ የሙያን ስነ-ምግባር በተላበሰ ሁኔታ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ገልፀዋል።
ስልጠናው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ፍስሃ ክፍሌ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ