ትውልዱ እየተገበረ ባለው የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህል የሴቶች አደረጃጀት አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
“በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የባስኬቶ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ በወሰን ተሻጋሪ በጎ አገልግሎት በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ የችግኝ ተከላና የአቅመ ደካማ እናት ቤት ግንባታን አስጀምረዋል።
የአሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ስመኝ ተስፋዬ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በጎ ተግባር አንድነትና የእርስ በርስ ግንኙነትን በማጠናከር ለሌሎች የምንደርስበት አንዱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢንሼቲቭ መሆኑን አንስተው የባስኬቶ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ስላደረጉት ሰው ተኮር ተግባር አመስግነዋል።
በጎ ተግባር በምድር ብቻ ሳይሆን በሰማይም ዋጋ ስላለው አቅመ ደካማ እናቶችን መርዳት የሁሉም ተግባር ሊሆን ይገባል ያሉት የባስኬቶ ዞን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ አስቴር ሰነቀ ናቸው።
የባስኬቶ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ መብቴ ግሮ እንዳስረዱት፤ “በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል ትውልዱ እየተገበረ ባለው የመደጋገፍና የመረዳዳት ባህል በሴቶች ክንፍ የተከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል።
የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሲሳይ ጋልሺ፤ የባስኬቶ ብሄር ከወንድም አሪ ሕዝብ ጋር የጠበቀ ቁርኝት መኖሩን ተናግረው ይህን አንድነትና ወንድማማችነትን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሠሩ ተናግረዋል።
በሴቶች የወሰን ተሻጋሪ በጎ አገልግሎት ቤት የተገነባላቸው እናትም በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልፀው ምስጋናቸውንም አቅርበዋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ