በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ የባስኬቶ ዞን ወጣቶች ክንፍ “በጎነት ለአብሮነትና ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል በኣሪ ዞን ጂንካ ከተማ ወሰን ተሻጋሪ በጎ ተግባራት አከናዉነዋል።
የበጎ አድራጎቱ ቡድኑ በቆይታው የችግኝ ተከላ፣ የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታና የቤት ቁሳቁስ ድጋፍና ለተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ያተበረከ ሲሆን በጂንካ ከተማ የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ጉብኝት አካሂዷል።
የኣሪ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማናኩል ሳህሎ በመርሃ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች እያከናወኑት ያለዉ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ አገልግሎት ተግባር የሀገራችን ከፍታና ማንሰራራትን የሚያጎሉ ስለሆኑ ሊበረታቱ እንደሚገባ ገልፀው የባስኬቶ ዞን ወጣቶች በዞኑ መጥተዉ ላከናወኑት የበጎ ተግባር ስራዎች አመስግነዋል።
የበጎ ተግባር አገልግሎት መልካም ተግባራትን ከማከናወን ባሻገር የእርስ በርስ ግንኙነትን የሚያጠናክር በመሆኑ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህላችንን በሚገባ ልናሰፋው ይገባል ያሉት የባስኬቶ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ክንዴ ፍሬዉ ናቸው።
የባስኬቶና የኣሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ዕድሉ ከበደ እና አቶ እስራኤል አዳሙ በጋራ እንደገለፁት፤ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መልካም ተሞክሮዎችን በማስፋት የበለፀገች ሀገር ለመገንባትና አንድነትን ለማጠናከር ስለሚያግዝ በትኩረት እንደሚሠሩ ተናግረዋል።
ወጣቶች የማህበረሰቡን አንድነትና ሕብረትን ለማጠናከር ምሳሌ በመሆን ጊዜውንና ጉልበቱን ለመልካም ተግባር ማዋል እንዳለበት በበጎ አገልግሎቱ የተሳተፉ ወጣቶች ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ