በ2025ቱ የቶኪዮ ዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች 1500 ሜትር ከኢትዮጵያ ብቸኛ ተወካይ የሆነችው አትሌት ፍሬወይኒ ወደ ፍፃሜው ማለፍ ችላለች።
በመጀመሪያው ምድብ ሆና የግማሽ ፍፃሜ ውድድሯን ያከናወነችው አትሌቷ ምንም እንኳን በውድድሩ መኃል ተደናቅፋ ወድቃ የነበረ ቢሆንም ከወደቀችበት ተነስታ በመሮጥ ውድድሯን በሶስተኝነት አጠናቃ ወደ ፍፃሜው መሻገሯን አረጋግጣለች።
የ1500 ሜትር ሴቶች ፍፃሜ ውድድር የፊታችን ማክሰኞ ከቀኑ 10 ሰዓት ከ05 ደቂቃ ላይ የሚካሄድ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የወጣቶችን አካላዊና አዕምሮዊ ጤና ለመጠበቅ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ5 ተከታታይ የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው የአርሰናል ተጫዋች ሆነ
ጆሿ ዚርኪዜ በሮማ ይፈለጋል