የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በቦንጋ ከተማ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት አካል የሆነውን እና 2.34 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የኮሪደር ልማት ጎበኙ፡፡
በከተማው እየተከናወነ የሚገኘው ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ የተሻለ ደረጃ ላይ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝቱ ወቅት ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም አንስተዋል።
ግንባታውን በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በአጠቃላይ ፕሮጀክቱ ከ75 በመቶ በላይ መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን በቀጣይ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታን ጨምሮ የሳይት ማፅዳትና ድልድዮችን የማጠናቀቁ ስራ እንደሚከናወን ተመላክቷል፡፡
በጉብኝቱ የክልሉ፣ የካፋ ዞንና የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ