የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በቦንጋ ከተማ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት አካል የሆነውን እና 2.34 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የኮሪደር ልማት ጎበኙ፡፡
በከተማው እየተከናወነ የሚገኘው ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ የተሻለ ደረጃ ላይ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝቱ ወቅት ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም አንስተዋል።
ግንባታውን በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በአጠቃላይ ፕሮጀክቱ ከ75 በመቶ በላይ መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን በቀጣይ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታን ጨምሮ የሳይት ማፅዳትና ድልድዮችን የማጠናቀቁ ስራ እንደሚከናወን ተመላክቷል፡፡
በጉብኝቱ የክልሉ፣ የካፋ ዞንና የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
ምክር ቤቱ በጋሞ ዞን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ3 ሚላዮን ብር ድጋፍ አደረገ
የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙ የበና ጸማይ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በክልሉ ከቱሪዝሙ ዘርፍ ባለፉት 9 ወራት 925.6 ሚሊዮን ብር ተገኝቷል