የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በቦንጋ ከተማ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት አካል የሆነውን እና 2.34 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የኮሪደር ልማት ጎበኙ፡፡
በከተማው እየተከናወነ የሚገኘው ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ የተሻለ ደረጃ ላይ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝቱ ወቅት ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም አንስተዋል።
ግንባታውን በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በአጠቃላይ ፕሮጀክቱ ከ75 በመቶ በላይ መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን በቀጣይ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታን ጨምሮ የሳይት ማፅዳትና ድልድዮችን የማጠናቀቁ ስራ እንደሚከናወን ተመላክቷል፡፡
በጉብኝቱ የክልሉ፣ የካፋ ዞንና የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን
More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የበለፀገች ሀገር ለመገንባትና አንድነትን ለማጠናከር አጋዥ መሆኑ ተገለፀ
የዘንድሮው የሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ “ያሆዴ” በዓል ሲከበር የተቸገሩትን በመደገፍ፣ በመተሳሰብ እና ያለውን ተካፍሎ በመብላት ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ኘሮጀክት አስተባባሪዎች እና የግብርና ሚንስቴር ብሔራዊ ኘሮጀክት ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ