የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በቦንጋ ከተማ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት አካል የሆነውን እና 2.34 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የኮሪደር ልማት ጎበኙ፡፡
በከተማው እየተከናወነ የሚገኘው ሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ የተሻለ ደረጃ ላይ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝቱ ወቅት ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩንም አንስተዋል።
ግንባታውን በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በአጠቃላይ ፕሮጀክቱ ከ75 በመቶ በላይ መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን በቀጣይ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታን ጨምሮ የሳይት ማፅዳትና ድልድዮችን የማጠናቀቁ ስራ እንደሚከናወን ተመላክቷል፡፡
በጉብኝቱ የክልሉ፣ የካፋ ዞንና የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳንኤል መኩሪያ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ