ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ለአሸናፊነት የሚጠበቁበት የሴቶች 10 ሺህ ሜትር የፍፃሜ ውድድር ዛሬ ይካሄዳል
በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለሜዳልያ አሸናፊነት የሚጠበቁበት የሴቶች 10 ሺህ ሜትር የፍፃሜ ውድድር በዛሬው ዕለት ከቀኑ 9:30 ይካሄዳል።
በውድድሩ ኢትዮጵያ በአራት አትሌቶች ትወከላለች።
አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ፣ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ፣ አትሌት ፎትየን ተስፋይ እና አትሌት ፅጌ ገብረሰላማ ኢትዮጵያን በመወከል ይወዳደራሉ።
በተጨማሪ በሻምፒዮናው በመክፈቻ ቀኑ ውሎ የ3 ሺህ ሜትር መሠናክል ወንዶች 6:05 እና በ1500 ሜትር የሴቶች ውድድር ከቀኑ 7:50 የማጣሪያ ውድድሮች ይከናወናሉ።
ዘጋቢ: ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የአንደኛ ደረጃ አትሌትክስ አሰልጣኞች ተመረቁ
ማንቸስተር ሲቲ ኤሊዮት አንደርሰንን የክለቡ ክብረ ወሰን በሆነ ዋጋ ለማስፈረም ተስማማ
ሶስቱ ብቸኛ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች