ካርሎስ አልካሬዝ የዓለማችን ቁጥር አንድ የሜዳ ቴኒስ ተጫዋች ሆነ
ስፔናዊው የሜዳ ቴኒስ ተጫዋች ካርሎስ አልካሬዝ የዩኤስ ኦፕን ውድድርን ማሸነፉን ተከትሎ የዓለማችን ቁጥር አንድ የሜዳ ቴኒስ ደረጃን መያዝ ችሏል።
ካርሎስ አልካሬዝ በዩኤስ ኦፕን የሜዳ ቴኒስ ፍፃሜ አራት ዙር በፈጀው ውድድር ጣሊያናዊውን ጃኒክ ሲነርን 6 – 3፣ 3 – 6፣ 6 – 1 እና 6 – 4 በማሸነፍ 6ኛውን የግራንድ ስላም በእጁ አስገብቷል።
የ22 ዓመቱ የሜዳ ቴኒስ ተጫዋች የግራንድ ስላምን 6 ጊዜ በማሸነፍ በዕድሜ ትንሹ ተወዳዳሪ ሆኗል።
ካርሎስ አልካሬዝ ከዓለማችን ዋና ዋና የሜዳ ቴኒስ ውድድሮች መካከል የፍሬንች ኦፕን፣ ዊምብልደንን እና ዩኤስ ኦፕንን እያንዳንዳቸውን ሁለት ጊዜ አሸናፊም ሆኗል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
“ማሬስካም ቢሆን እንደ ፔፕ ድንቅ ነው” ሚኬል አርቴታ
የፒኤስጂው ኮከብ ኪቪቻ ክቫራትስኬሊያ አዲስ ወኪል መረጠ!
የክረምት እግር ኳስ ሻምፒዮናው የተሻለ አቅም ያላቸው ተተኪ ስፖርተኞችን የምናፈራበት ነው – የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር