የህብር ቀን “ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ ሐሣብ በማዕከላዊ ኢትዮያውያ ክልል ሣጃ ክላስተር እየተከበረ ነው
የጳጉሜን ቀናትን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት የተለያዩ ስያሜዎችን በመሠየም ልዩ ትኩረት ሠጥቶ እየሠራ ነው ።
ዘንድሮም ጰጉሜ ሁለትን የሕብር ቀን በማለት ብሔራዊ አንድነትን አብሮነትንና ብዙ ሆነው በአንድ ሀሣብ ማደግን መሠረት በማድረግ እየተከበረ ይገኛል።
በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ሣጃ ክላስተር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የክላስተሩ የዞኑ እና ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የሣጃ ዙሪያ አመራሮችና ሠራተኞች በወንድማማችች አደባባይ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የእግር ጉዞ በማድረግ የሣጃ ከተማን የልማት ሥራዎች ጉብኝት ተደርገዋል።
ቀኑን አስመልክቶ የተለያዩ ባህላዊ ቁሣቁሦች ኤግዝቢሽን እና የደም ልገሣ መርሃ ግብር የተከናወነ ሲሆን የፓናል ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ማሙዬ ፊጣ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለተለያዩ አገልግሎት ያስገነባቸውን ዘመናዊ ኮምፕሌክሶችን አስመረቀ
በጎፋ ዞን ወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የበጋ ማጠቃለያና የክረምት በጎ ስራ ማስጀመሪያ መረሃ-ግብር ተካሄደ
በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን ሀብት መሰብሰብ መቻሉ ተገለጸ