የህብር ቀን “ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ ሐሣብ በማዕከላዊ ኢትዮያውያ ክልል ሣጃ ክላስተር እየተከበረ ነው
የጳጉሜን ቀናትን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት የተለያዩ ስያሜዎችን በመሠየም ልዩ ትኩረት ሠጥቶ እየሠራ ነው ።
ዘንድሮም ጰጉሜ ሁለትን የሕብር ቀን በማለት ብሔራዊ አንድነትን አብሮነትንና ብዙ ሆነው በአንድ ሀሣብ ማደግን መሠረት በማድረግ እየተከበረ ይገኛል።
በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ሣጃ ክላስተር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የክላስተሩ የዞኑ እና ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የሣጃ ዙሪያ አመራሮችና ሠራተኞች በወንድማማችች አደባባይ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የእግር ጉዞ በማድረግ የሣጃ ከተማን የልማት ሥራዎች ጉብኝት ተደርገዋል።
ቀኑን አስመልክቶ የተለያዩ ባህላዊ ቁሣቁሦች ኤግዝቢሽን እና የደም ልገሣ መርሃ ግብር የተከናወነ ሲሆን የፓናል ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ማሙዬ ፊጣ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ