የህብር ቀን “ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ ሐሣብ በማዕከላዊ ኢትዮያውያ ክልል ሣጃ ክላስተር እየተከበረ ነው
የጳጉሜን ቀናትን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት የተለያዩ ስያሜዎችን በመሠየም ልዩ ትኩረት ሠጥቶ እየሠራ ነው ።
ዘንድሮም ጰጉሜ ሁለትን የሕብር ቀን በማለት ብሔራዊ አንድነትን አብሮነትንና ብዙ ሆነው በአንድ ሀሣብ ማደግን መሠረት በማድረግ እየተከበረ ይገኛል።
በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ሣጃ ክላስተር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የክላስተሩ የዞኑ እና ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የሣጃ ዙሪያ አመራሮችና ሠራተኞች በወንድማማችች አደባባይ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የእግር ጉዞ በማድረግ የሣጃ ከተማን የልማት ሥራዎች ጉብኝት ተደርገዋል።
ቀኑን አስመልክቶ የተለያዩ ባህላዊ ቁሣቁሦች ኤግዝቢሽን እና የደም ልገሣ መርሃ ግብር የተከናወነ ሲሆን የፓናል ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ማሙዬ ፊጣ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ