የህብር ቀን “ብዝሃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ ሐሣብ በማዕከላዊ ኢትዮያውያ ክልል ሣጃ ክላስተር እየተከበረ ነው
የጳጉሜን ቀናትን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት የተለያዩ ስያሜዎችን በመሠየም ልዩ ትኩረት ሠጥቶ እየሠራ ነው ።
ዘንድሮም ጰጉሜ ሁለትን የሕብር ቀን በማለት ብሔራዊ አንድነትን አብሮነትንና ብዙ ሆነው በአንድ ሀሣብ ማደግን መሠረት በማድረግ እየተከበረ ይገኛል።
በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ሣጃ ክላስተር ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የክላስተሩ የዞኑ እና ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የሣጃ ዙሪያ አመራሮችና ሠራተኞች በወንድማማችች አደባባይ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና የእግር ጉዞ በማድረግ የሣጃ ከተማን የልማት ሥራዎች ጉብኝት ተደርገዋል።
ቀኑን አስመልክቶ የተለያዩ ባህላዊ ቁሣቁሦች ኤግዝቢሽን እና የደም ልገሣ መርሃ ግብር የተከናወነ ሲሆን የፓናል ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ማሙዬ ፊጣ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ