ጳጉሜን 1 – የጽናት ቀን “ጽኑ መሠረት ብርቱ ሀገር” በሚል መሪ ቃል በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ እየተከበረ ነው።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የካፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ደመላሽ ንጉሴ፤ ሀገራዊ ለውጥ ከመጣ ወዲህ በተለያዩ ስያሜዎች የጳጉሜን ወር ማክበር እየተለመደ መጥቷል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በርካታ ችግሮችን ተሻግራ በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና በማህበራዊ ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን በማሰብ የተሻለ ነገን መፍጠር ላይ ማተኮር እንደሚገባ ገልጸዋል።
የዘንድሮው የጳጉሜ ወር የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የሚበሰርበት ወቅት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ያሉት አቶ ደመላሽ፤ የዚህ ድል ባለቤት በመሆናችን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
ጳጉሜን 1 የጽናት ቀኑ ተብሎ የመከበሩ ዋና ምክንያት ጽናት ለሀገር ሁለንተናዊ ለውጥ መሠረት በመሆኑ ነው ብለዋል።
በጽናት የሚቆም ትውልድ ሀገርን በመገንባት ቀጣይነትን እንደሚያረጋግጥ ተናግረዋል።
በጽናት የሚቆም ትውልድ በአቋም በመታገል ለሀገር ቅድሚያ ይሰጣል ብለዋል።
የጽናት ቀን ሲከበር ለኢትዮጵያ ለሰላምና ለደህንነት የታገሉና የተዋደቁትን በማሰብና በማመስገን ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመድረኩ ዕለቱን በተመለከተ የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰብስቤ ሻዎኖ በበኩላቸው፤ ጽናት ከግለሰብ እንደሚጀምር ጠቁመው የጸና ቤተሰብ የጸናች ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ነው ብለዋል።
ፈተናዎችን ተሻግሮ ሀገርን ለትውልድ ለማስረከብ ጸንቶ መቆምን እንደሚጠይቅ አንስተዋል።
ዘጋቢ፡ ሀብታሙ ታደሰ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ