“ጽኑ መሰረት ብርቱ ሀገር” በሚል መሪ ቃል ጳጉሜን 1 ‘የጽናት ቀን’ በጎፋ ዞን በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።
የሣውላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶ/ር ንጉሴ መኮንን፤ ከለውጡ ማግስት ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ ችግሮች ቢያጋጥሟትም ባለፉት ሰባት ዓመታት በጽናት በመታገል በርካታ ድሎች ማስመዝገቧን ተናግረው በቀጣይ በከተማው የተጀመሩ የልማት ሥራዎች በጽናትና በአንድነት የምንተገብርበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በዕለቱን መልዕክት ያስተላለፉት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን ለምረቃ ጥቂት ቀናት በቀረበት ወቅት የጽናት ቀን መከበሩ ደስታችንን እጥፍ ያደርገዋል ብለዋል፡፡
ግድቡ የሀገር ኩራት ምልክት፣ የህዝቡ የጽናት ማሳያ መሆኑን ገልጸው እንደ ዞን ከለውጡ ማግስት ወዲህ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት በአካባቢያችን የተጀመሩ መሰረተ ልማቶችና በኢኮኖሚው ዘርፍ የተመዘገቡ ለውጦች የአንድነትና የጽናት ውጤት እንደሆኑም ተናግረዋል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊና የሣውላ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አቤነዘር ተረፈ፤ አባቶቻችን ትላንት አደዋ ላይ ድል ያደረጉበትን ዛሬ በአንድነት እና በጽናት በልማት ሥራዎቻችን በመድገም በክልላችን የተመዘገቡ ውጤቶችና ስኬቶች የፅናታችን መገለጫ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ የተለያዩ የፖሊስ ትዕይቶችና የኢትዮጵያ ብሔራዊ የህዝብ መዝሙር ቀርቦ ተጠናቋል።
ዘጋቢ: ስንታየሁ ሙላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የሰራተኞች የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ብዙዎችን የቤት ባለቤት ማድረጉ ተገለጸ
በሁሉም ዘርፎች እንደሀገር አመርቂ ውጤቶች እየተዘመገቡ ነው – የቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች
የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓትን በማዘመን የመረጃ ታማኝነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ