ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ተስማማ
ማንቸስተር ዩናይትድ የሮያል አንትወርፑን ግብ ጠባቂ ሴኔ ላሜንስ ለማስፈረም ከስምምነት ላይ ደርሷል።
የዚህ ውድድር ዓመት አጀማመር ያላማረለት ማንቸስተር ዩናይትድ ቤልጂየማዊውን ግብ ጠባቂ በ21 ሚልዮን ዩሮ እና ተጨማሪ ክፍያ ለማስፈረም መስማማቱን የፋብሪዚዮ ሮማኖ መረጃ አመላክቷል።
የ23 ዓመቱ ግብ ጠባቂ በዛሬው ዕለት የጤና ምርመራው ካጠናቀቀ በኋላ የ5 ዓመት ኮንትራት ከቀያይ ሰይጣኖች ጋር ይፈራረማል ተብሎ ይጠበቃል።
ሴኔ ላሜንስ ባለፈው የውድድር ዓመት በ30 የቤልጅየም ፕሮ ሊግ ጨዋታዎች የተሰለፈ ሲሆን በ7 መርሐግብሮች ጎል ሳይቆጠርበት ከሜዳ ወጥቷል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የአንደኛ ደረጃ አትሌትክስ አሰልጣኞች ተመረቁ
ማንቸስተር ሲቲ ኤሊዮት አንደርሰንን የክለቡ ክብረ ወሰን በሆነ ዋጋ ለማስፈረም ተስማማ
ሶስቱ ብቸኛ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች