ሉካስ ቫዝኩዌዝ ወደ ባዬርሊቨርኩሰን ሊያመራ ነው
ከሪያል ማድሪድ ጋር ያለው የውል ዘመን መጠናቀቁን ተከትሎ ከ10 ዓመታት በኋላ የሎስብላንኮዎቹን ቤት የለቀቀው ሉካስ ቫስኩዌዝ ወደ ጀርመኑ ክለብ ባዬርሊቨርኩሰን ለማቅናት መቃረቡ ተገልጿል።
ስፔናዊው ሁለገብ ተጫዋች የአሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሃጉን ቡድን በሁለት ዓመት ውል ለመቀላቀል ከስምምነት ላይ መድረሱን ማርካ አስነብቧል።
የ34 ዓመቱን ተጫዋች ለማስፈረም በዋናነት የስፔኑ ክለብ ዲፖርቲቮላካሩኛ ፍላጎት ቢያሳይም ከሪያል ማድሪድ ጋር በሌላ ክለብ ማልያ ላለመገናኘት ሲል የዝውውር ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ ተነግሯል።
ሉካስ ቫዝኩዌዝ በሪያል ማድሪድ በቆየባቸው ጊዜያት ከ400 በላይ ጨዋታዎችን በማከናወን 5 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ እና 4 የስፔን ላሊጋ ዋንጫዎችን ጨምሮ 20 ዋንጫዎችን መሳም ችሏል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የአንደኛ ደረጃ አትሌትክስ አሰልጣኞች ተመረቁ
ማንቸስተር ሲቲ ኤሊዮት አንደርሰንን የክለቡ ክብረ ወሰን በሆነ ዋጋ ለማስፈረም ተስማማ
ሶስቱ ብቸኛ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች