በደቡብ ኦሞ ዞን ማሌ ወረዳ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሀ-ግብር ቤት የተገነባላቸዉ አካላት መደሰታቸውን ገለፁ
ወረዳዉ የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩን በማሻላ ቀበሌ አካሂዷል።
የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባሊንሠ እንዳሉት፤ በአጠቃላይ በወረዳው ሁሉም ቀበሌያት 116 ቤቶችን ሠርቶ ለአቅመ ደካሞች ለማስረከብ አቅዶ እየተራ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ በዚሁም ወደ አሥር ሚሊዮን ብር ለማዳን መታቀዱንም አስረድተዋል።
የደቡብ ኦሞ ዞን ደንና አካባቢ ጥበቃ መምሪያ ሀላፊ አቶ ያምላክስራ ናደው በበኩላቸው፤ አቅመ ደካሞችን የመደገፉ ስራ 960 ቤቶች እንደዞን እንደሚገነባና በዛሬዉ ዕለት በይፋ የተጀመረውን እስከ መጨረሻ ድረስ በማስቀጠል ባጭር ጊዜ በማጠናቀቅ አቅመ ደካሞቹን ተጠቃሚ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ቤት የተገነባላቸዉ አቅመ ደካሞች በወረዳዉ የማሻላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ ሞትዞ ማቶ፣ ጊማቶ ግርማ እና አቶ ለማ ባልኦ በጋራ በሰጡት አስተያየት፤ መንግስትና ህዝብ በተባበረ ክንድ ላደረጉት ደጋፍ አመስግነው መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዳኛቸዉ ደሴ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ