የክረምት ዝናብን ተከትሎ ጎርፍ እና መሰል አደጋዎች በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እንዳያስከትሉ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ
ከጎርፍና መሰል አደጋዎች ባሻገር የከሰል እሳት አጠቃቀምም ላይ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ መምሪያው ጠቁሟል።
የዘንድሮው የክረምት ዝናብ ጠንከር ያለና ቀጣይነት ያለው መሆኑን የአየር ትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደርሶ በላይ፤ ሰሞኑን እየጣለ ባለው ዝናብ ምክንያት የመሬት መሸርሸር፣ ናዳ እና ጎርፍ ሊከሰት ስለሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች ልየታ በማድረግ ለአደጋ ተጋላጭ አካባቢዎች ላይ የሚገኙ አካላት እንዲነሱ በማድረግ የቅድመ ጥንቃቄ ስራ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
የውሃ ማፋሰሻ ቦዮችን በማፅዳትና ለጎርፍ መውረጃ ማዘጋጀት ይገባል ያሉት አቶ ደርሶ፤ ቆላማ አካባቢዎች ላይ ዝናብ ባይጥል እንኳ ወንዞች በደራሽ ዉሃ መሞላት ሊያጋጥም ስለሚችል ህፃናት ወደ ወንዝ እንዳይሄዱ መጠበቅ እንደሚገባም አስታውቀዋል።
አያይዘውም በክረምት ወራት ብርድን ለመከላከል ተብሎ ጥንቃቄ የጎደለው የከሰል እሳት መጠቀም ለሞት ስለሚዳርግ ከቤት ውጪ ከሰል ማቀጣጠል፣ በቤት ውስጥም በቂ አየር እንዲገባ በማድረግ ሊፈጠር ከሚችል አደጋ ራስን መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በመንግስት ድጋፍና በህብረተሰቡ ተሣትፎ የተገነባው ጤና ጣቢያ በጎፋ ዞን ደንባ ጎፋ ወረዳ ወይዴ ውርኪ ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
በትራንስፕርት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ እየተደረገ ባለው ከታሪፍ በላይ ጭማሪ ለተለያዩ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች እየተጋለጥን ነው ሲሉ በወልቂጤ ከተማ መናኽሪያ አግኝተን ያነጋገርናቸው ተሳፋሪዎች ተናገሩ
የሳውላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ወንጀልን የሚጸየፉ አምራች ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገለፀ