የክረምት ዝናብን ተከትሎ ጎርፍ እና መሰል አደጋዎች በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት እንዳያስከትሉ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ
ከጎርፍና መሰል አደጋዎች ባሻገር የከሰል እሳት አጠቃቀምም ላይ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ መምሪያው ጠቁሟል።
የዘንድሮው የክረምት ዝናብ ጠንከር ያለና ቀጣይነት ያለው መሆኑን የአየር ትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደርሶ በላይ፤ ሰሞኑን እየጣለ ባለው ዝናብ ምክንያት የመሬት መሸርሸር፣ ናዳ እና ጎርፍ ሊከሰት ስለሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች ልየታ በማድረግ ለአደጋ ተጋላጭ አካባቢዎች ላይ የሚገኙ አካላት እንዲነሱ በማድረግ የቅድመ ጥንቃቄ ስራ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
የውሃ ማፋሰሻ ቦዮችን በማፅዳትና ለጎርፍ መውረጃ ማዘጋጀት ይገባል ያሉት አቶ ደርሶ፤ ቆላማ አካባቢዎች ላይ ዝናብ ባይጥል እንኳ ወንዞች በደራሽ ዉሃ መሞላት ሊያጋጥም ስለሚችል ህፃናት ወደ ወንዝ እንዳይሄዱ መጠበቅ እንደሚገባም አስታውቀዋል።
አያይዘውም በክረምት ወራት ብርድን ለመከላከል ተብሎ ጥንቃቄ የጎደለው የከሰል እሳት መጠቀም ለሞት ስለሚዳርግ ከቤት ውጪ ከሰል ማቀጣጠል፣ በቤት ውስጥም በቂ አየር እንዲገባ በማድረግ ሊፈጠር ከሚችል አደጋ ራስን መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
”ሠላምን ማፅናት ለክልሉ ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ መካሔድ ጀመረ
የህዳሴው ግድብ ኢትዮጵያውያን በአንድነት ያሳኩት የጋራ ድል መሆኑን የጨታ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ
በዶሮ እርባታ ስራ በመሰማራታቸው የገቢ ምንጫቸውን ከማሳደግ ባሻገር ለሌሎችም የሥራ እድል መፍጠር መቻላቸውን በአርባምንጭ ከተማ የሚገኙ ማህበራት ገለጹ