በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ የአንድ ጀምበር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተካሄደ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) “በጎነት ለአብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ ተካሂዷል፡፡
የሣላማጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ህጉ ቅጣቱ ፤ የአንድ ጀምበር የአረጋዊያንና አቅመ ደካማ ቤት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በገሮ ቀበሌ አካሂደዋል።
በ2017 ዓ.ም በክረምቱ ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር እንደ ወረዳ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ የሚገኙ ሲሆን ዛሬ የሚጀመረው የአንድ ጀምበር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በእጅጉ የሚያሳድግ ነው ብለዋል አስተዳዳሪው።
የሳላማጎ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሠረት አስፋው እንደገለፁት፤ በክረምቱ ከሚከናወኑ መደበኛ ተግባራት ውጪ በወረዳው ባሉ ቀበሌያት ሁሉ 42 አዲስ ቤት ግንባታና 42 ዕድሳት በድምሩ 84 ቤቶችን በአንድ ቀን ጀንበር ለአቅመ ደካሞች ለመገንባት ወደ ተግባር መገባቱን ገልፀዋል።
ኃላፊው አክለውም በንቅናቄ በሚሰራው ሥራ እንደ ወረዳ 8 ሺህ 580 በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ 18 ሺህ 850 በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ በማድረግ 6 ሚሊየን 345 ሺህ 798 ብር ከመንግስት የሚወጣን ገንዘብ ለማዳን ታቅዶ እየተሠራ ነው።
የየቀበሌው ሊቀመናብርትና ወጣቶች መካከል አቶ ያረድ ወጽቶ፣ ገረሙ ዝጳን፣ ጳውሎስ ወቃሱ ወጣት ሳምኤል ባካንና ሌሎችም በአንድ ቀን ጀምበር ለሚከናወነው የአቅመ ደካማዎች ቤት ግንባታ በወጣቱ የነቃ ተሳትፎ እና በማህበረሰቡ በጎ ትብብር በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በደቡብ ኦሞ ዞን ማሌ ወረዳ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሀ-ግብር ቤት የተገነባላቸዉ አካላት መደሰታቸውን ገለፁ
ሁሉ አቀፍ ድጋፍ የሚሹ አካላትን መርዳት የጥቂት አካላት ተግባር ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሥራ ሊሆን እንደሚገባ ተገለፀ
የዲላ ከተማ አስተዳደር የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በአንድ ጀምበር ቤቶች ግንባታ መርሐ ግብር በጎላ ቀበሌ በይፋ ተጀመረ