በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ የአንድ ጀምበር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተካሄደ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) “በጎነት ለአብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በደቡብ ኦሞ ዞን ሳላማጎ ወረዳ ተካሂዷል፡፡
የሣላማጎ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ህጉ ቅጣቱ ፤ የአንድ ጀምበር የአረጋዊያንና አቅመ ደካማ ቤት ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በገሮ ቀበሌ አካሂደዋል።
በ2017 ዓ.ም በክረምቱ ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባር እንደ ወረዳ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ የሚገኙ ሲሆን ዛሬ የሚጀመረው የአንድ ጀምበር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በእጅጉ የሚያሳድግ ነው ብለዋል አስተዳዳሪው።
የሳላማጎ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሠረት አስፋው እንደገለፁት፤ በክረምቱ ከሚከናወኑ መደበኛ ተግባራት ውጪ በወረዳው ባሉ ቀበሌያት ሁሉ 42 አዲስ ቤት ግንባታና 42 ዕድሳት በድምሩ 84 ቤቶችን በአንድ ቀን ጀንበር ለአቅመ ደካሞች ለመገንባት ወደ ተግባር መገባቱን ገልፀዋል።
ኃላፊው አክለውም በንቅናቄ በሚሰራው ሥራ እንደ ወረዳ 8 ሺህ 580 በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ 18 ሺህ 850 በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ በማድረግ 6 ሚሊየን 345 ሺህ 798 ብር ከመንግስት የሚወጣን ገንዘብ ለማዳን ታቅዶ እየተሠራ ነው።
የየቀበሌው ሊቀመናብርትና ወጣቶች መካከል አቶ ያረድ ወጽቶ፣ ገረሙ ዝጳን፣ ጳውሎስ ወቃሱ ወጣት ሳምኤል ባካንና ሌሎችም በአንድ ቀን ጀምበር ለሚከናወነው የአቅመ ደካማዎች ቤት ግንባታ በወጣቱ የነቃ ተሳትፎ እና በማህበረሰቡ በጎ ትብብር በጥሩ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ