የዲላ ከተማ አስተዳደር የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በአንድ ጀምበር ቤቶች ግንባታ መርሐ ግብር በጎላ ቀበሌ በይፋ ተጀመረ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 19/2017 ዓ፣ም (ደሬቴድ) “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ አስተዳደር የ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በአንድ ጀንበር ቤቶች ግንባታ መርሐ ግብር በጎላ ቀበሌ በይፋ ተጀምሯል፡፡
መርሐ ግብሩን ያስጀመሩት የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶክተር መስፍን ደምሴ፤ በከተማ አስተዳደሩ በአስር ቀበሌያት በአንድ ጀንበር ሶስት መቶ ቤቶች ለመገንባት ማቀዳቸውን ተናግረዋል።
የአንድ ጀምበር መርሀ ግብር ለ2 ሺህ 5 መቶ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ያሉት ከንቲባው፤ 10 ሚሊዮን ብር ከመንግስት ካዜና ይወጣ የነበረን ወጪ ለማዳን ዕቅድ መያዛቸውን አብራርተዋል።
ቤት ከመሠረታዊ ፍላጎቶች አንደኛውና ወሳኝ በመሆኑ ከክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ባሻገር በዲላ ከተማ ለነዋሪዎቹ በቂ ቤት የመገንባት ሥራ እየተሠራ ነው ብለዋል።
የአንድ ጀንበር የቤቶች ግንባታ በንግድ፣ በመንግሥት ሰራተኞች፣ በወጣቶች እና በተለያዩ ዘርፎች ላይ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማስተባበር እየተሠራ መሆኑን የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መንግስቱ ተክሌ ተናግረዋል።
የዲላ ከተማ አስተዳደር ስፖርት እና ወጣቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መላኩ አየለ፤ በጎነት ከራስ ለራስ የሚደረግ ተግባር በመሆኑ በከተማ አስተዳደር ወጣቶች በንቃት እየተሳተፉበት መሆናቸውን ገልጸዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የአንዲዳ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቶ ማሙሽ ታሪኩ እና ወይዘሮ ትዕግስት ሰራዊት ከዚህ ቀደም ቤታቸው በማርጀቱ በዝናብ እና በጎርፍ ሲቸገሩ መቆየታቸውን አንስተው በተደረገው ድጋፍ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ዘጋቢ: አሀዱ አሸናፊ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ