በገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም አፈፃፀም ዙሪያ በሆሳዕና ከተማ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም አፈፃፀም ዙሪያ የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ከተረጂነት ለመውጣት በተቀናጀ ግብርና በተሰራው ስራ በተረጂዎች ላይ የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት መቻሉን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ማዕረጉ ማቲዎስ አስታውቀዋል።
በክልሉ በ 35 ወረዳዎች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተሰራው ልማታዊ ሴፍትኔት ከ 318 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ መሆናቸው አመላክተዋል።
በተጠናቀቀው በጀት አመት ተቋሙ የገጠመውን የፋይናንስ ችግር ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራው ስራ ህብረተሰቡ ወደ ምርታማነት መቀየር ተችሏል።
በቀጣይም የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለማውጣት በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።
ዘጋቢ፡ ራሔል አሊ

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለአካባቢው ማህበረሰብ ለውጥ የሚበጅ፤ ዘመኑን በሚዋጅ የቴክኖሎጂ እውቀት የበለጸጉ ዜጎች የሚፈልቁበት ተቋም ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ
የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጥ የሚገድቡ እንቅፋቶችን በትብብር መፍታት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሀመድናስር ገለጹ