በገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም አፈፃፀም ዙሪያ በሆሳዕና ከተማ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም አፈፃፀም ዙሪያ የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ከተረጂነት ለመውጣት በተቀናጀ ግብርና በተሰራው ስራ በተረጂዎች ላይ የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት መቻሉን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ማዕረጉ ማቲዎስ አስታውቀዋል።
በክልሉ በ 35 ወረዳዎች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተሰራው ልማታዊ ሴፍትኔት ከ 318 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ መሆናቸው አመላክተዋል።
በተጠናቀቀው በጀት አመት ተቋሙ የገጠመውን የፋይናንስ ችግር ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራው ስራ ህብረተሰቡ ወደ ምርታማነት መቀየር ተችሏል።
በቀጣይም የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለማውጣት በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።
ዘጋቢ፡ ራሔል አሊ

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ