በገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም አፈፃፀም ዙሪያ በሆሳዕና ከተማ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 19/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም አፈፃፀም ዙሪያ የምክክር መድረክ በመካሄድ ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ከተረጂነት ለመውጣት በተቀናጀ ግብርና በተሰራው ስራ በተረጂዎች ላይ የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት መቻሉን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ማዕረጉ ማቲዎስ አስታውቀዋል።
በክልሉ በ 35 ወረዳዎች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር በተሰራው ልማታዊ ሴፍትኔት ከ 318 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ መሆናቸው አመላክተዋል።
በተጠናቀቀው በጀት አመት ተቋሙ የገጠመውን የፋይናንስ ችግር ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራው ስራ ህብረተሰቡ ወደ ምርታማነት መቀየር ተችሏል።
በቀጣይም የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለማውጣት በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።
ዘጋቢ፡ ራሔል አሊ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ