አሊያንስ ኮሌጅ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን በማፍራት የሀገሪቱን ዕድገት ለማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስታወቀ
ኮሌጁ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ800 በላይ ተማሪዎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል።
የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አዲሱ አዳሙ (ዶ/ር)፤ ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን ተሞክሮ የሚቀመርበት በመሆኑ በተቋሙ የተመረቁ ተማሪዎች ሥራ ፈላጊ ሳይሆኑ ሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።
የኮሌጁ ዲን አቶ ፋሲል ሰለሞን ለተመራቂዎቹ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሀገር ወዳድና የሰላም ባለቤት እንዲሆኑ እንዲሁም ማህበረሰባቸውን በትጋት እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።
ኮሌጁ በኢንፎርማቲክስና በቢዝነስ ፋኩልቲ በድግሪ መርሃ ግብር በመደበኛ፣ በማታና በርቀት 269 ተማሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በቢዝነስና አይሲቲ ዘርፍ 562 ተማሪዎችን በድምሩ 831 ተማሪዎችን አስመርቋል።
የዕለቱ ተመራቂዎች በመመረቃቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው፤ ማህበረሰባቸውን በትጋት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ አማሮ አርሳባ – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ