አሊያንስ ኮሌጅ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን በማፍራት የሀገሪቱን ዕድገት ለማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስታወቀ
ኮሌጁ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ800 በላይ ተማሪዎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል።
የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አዲሱ አዳሙ (ዶ/ር)፤ ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን ተሞክሮ የሚቀመርበት በመሆኑ በተቋሙ የተመረቁ ተማሪዎች ሥራ ፈላጊ ሳይሆኑ ሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።
የኮሌጁ ዲን አቶ ፋሲል ሰለሞን ለተመራቂዎቹ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሀገር ወዳድና የሰላም ባለቤት እንዲሆኑ እንዲሁም ማህበረሰባቸውን በትጋት እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።
ኮሌጁ በኢንፎርማቲክስና በቢዝነስ ፋኩልቲ በድግሪ መርሃ ግብር በመደበኛ፣ በማታና በርቀት 269 ተማሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በቢዝነስና አይሲቲ ዘርፍ 562 ተማሪዎችን በድምሩ 831 ተማሪዎችን አስመርቋል።
የዕለቱ ተመራቂዎች በመመረቃቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው፤ ማህበረሰባቸውን በትጋት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ አማሮ አርሳባ – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለአካባቢው ማህበረሰብ ለውጥ የሚበጅ፤ ዘመኑን በሚዋጅ የቴክኖሎጂ እውቀት የበለጸጉ ዜጎች የሚፈልቁበት ተቋም ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ
የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጥ የሚገድቡ እንቅፋቶችን በትብብር መፍታት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሀመድናስር ገለጹ