አሊያንስ ኮሌጅ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን በማፍራት የሀገሪቱን ዕድገት ለማፋጠን የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስታወቀ
ኮሌጁ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ800 በላይ ተማሪዎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል።
የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አዲሱ አዳሙ (ዶ/ር)፤ ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን ተሞክሮ የሚቀመርበት በመሆኑ በተቋሙ የተመረቁ ተማሪዎች ሥራ ፈላጊ ሳይሆኑ ሥራ ፈጣሪ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።
የኮሌጁ ዲን አቶ ፋሲል ሰለሞን ለተመራቂዎቹ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሀገር ወዳድና የሰላም ባለቤት እንዲሆኑ እንዲሁም ማህበረሰባቸውን በትጋት እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።
ኮሌጁ በኢንፎርማቲክስና በቢዝነስ ፋኩልቲ በድግሪ መርሃ ግብር በመደበኛ፣ በማታና በርቀት 269 ተማሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በቢዝነስና አይሲቲ ዘርፍ 562 ተማሪዎችን በድምሩ 831 ተማሪዎችን አስመርቋል።
የዕለቱ ተመራቂዎች በመመረቃቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው፤ ማህበረሰባቸውን በትጋት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ አማሮ አርሳባ – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ