በ2018 የትምህርት ዘመን ሁሉም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸዉ እንዲመጡ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረዉ መቀጠል ይኖርባቸዋል – የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻዉ ከበደ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ2018 የትምህርት ዘመን ሁሉም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸዉ እንዲመጡ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረዉ መቀጠል ይኖርባቸዋል ሲሉ የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻዉ ከበደ ገለጹ።
በዞኑ ባለፉት ጊዜያት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ቀጣይነት እንዲኖራቸዉ እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።
አቶ እንዳሻዉ የ2018 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ ብቁ፣ ተወዳዳሪና ሀገር የሚጠቅም ትዉልድ እንዲፈጠር የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸዉን ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት ማህበረሰቡን በማስተባበር ባለፈዉ የትምህርት ዘመን ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የትምህርት ጥራትን የሚያስጠብቁ ድጋፎች መደረጋቸዉን ገልጸዋል።
መሰል ተግባራት በ2018 የትምህርት ዘመን ቀጣይነት እንዲኖራቸዉና ትምህርት ቤቶች ለመማር ማስተማር ምቹ እንዲሆኑ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ስለሆነም ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡ በሚመለከታቸዉ አካላት የተጀሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረዉ ሊቀጥሉ ይገባቸዋል ብልዋል።
በ2018 የትምህርት ዘመን ከ3 መቶ 51 ሺ በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡ ግብ ተጥሉ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ እንዳሻዉ፤ የተማሪ ወላጆች፣ መምህራን፣ በየደረጃዉ ያሉ አመራሮችና የሚመለከታቸዉ አካላት እቅዱን ከግብ ለማድረስ በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
ከነሐሴ 19/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 5 ቀናት የሚቆየዉ የተማሪዎች ምዝገባ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ የመማር ማስተማሩን ስራ በጊዜ ለማስጀመር ሁሉም አካላት በኃላፊነት መንቀሳቀስ ያስፈልጋቸዋል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ትዕግስቱ ጴጥሮስ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለአካባቢው ማህበረሰብ ለውጥ የሚበጅ፤ ዘመኑን በሚዋጅ የቴክኖሎጂ እውቀት የበለጸጉ ዜጎች የሚፈልቁበት ተቋም ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ
የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጥ የሚገድቡ እንቅፋቶችን በትብብር መፍታት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሀመድናስር ገለጹ