በ2018 የትምህርት ዘመን ሁሉም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸዉ እንዲመጡ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረዉ መቀጠል ይኖርባቸዋል – የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻዉ ከበደ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ2018 የትምህርት ዘመን ሁሉም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸዉ እንዲመጡ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረዉ መቀጠል ይኖርባቸዋል ሲሉ የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻዉ ከበደ ገለጹ።
በዞኑ ባለፉት ጊዜያት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ቀጣይነት እንዲኖራቸዉ እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።
አቶ እንዳሻዉ የ2018 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ ብቁ፣ ተወዳዳሪና ሀገር የሚጠቅም ትዉልድ እንዲፈጠር የተለያዩ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸዉን ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት ማህበረሰቡን በማስተባበር ባለፈዉ የትምህርት ዘመን ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የትምህርት ጥራትን የሚያስጠብቁ ድጋፎች መደረጋቸዉን ገልጸዋል።
መሰል ተግባራት በ2018 የትምህርት ዘመን ቀጣይነት እንዲኖራቸዉና ትምህርት ቤቶች ለመማር ማስተማር ምቹ እንዲሆኑ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ስለሆነም ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡ በሚመለከታቸዉ አካላት የተጀሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረዉ ሊቀጥሉ ይገባቸዋል ብልዋል።
በ2018 የትምህርት ዘመን ከ3 መቶ 51 ሺ በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመጡ ግብ ተጥሉ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ እንዳሻዉ፤ የተማሪ ወላጆች፣ መምህራን፣ በየደረጃዉ ያሉ አመራሮችና የሚመለከታቸዉ አካላት እቅዱን ከግብ ለማድረስ በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
ከነሐሴ 19/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 5 ቀናት የሚቆየዉ የተማሪዎች ምዝገባ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ የመማር ማስተማሩን ስራ በጊዜ ለማስጀመር ሁሉም አካላት በኃላፊነት መንቀሳቀስ ያስፈልጋቸዋል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ትዕግስቱ ጴጥሮስ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ