ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ በኩል የምክር ቤቱ አባላት ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ተገለፀ
በዳውሮ ዞን ሎማ ቦሣ ወረዳ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 32ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።
የወረዳው ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አየለ አይኑ፥ ምክር ቤቱ ከፍተኛ የህዝብ ሥልጣን ባለቤት መሆኑን ተናግረው የህዝብ ሉዓላዊነት መግለጫ በመሆኑ፥ በመንግስት አሰራር ውስጥ የህዝብ ተሳትፎ የሚያረጋግጥ ተቋም ነው ብለዋል፡፡
ምክር ቤቱ የህዝብና የመንግስት ሀብትና ንብረት ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንድውል ቁጥጥርና ክትትል የሚያደርግ ተቋም እንደሆነ ገልጸው፥ በበጀት ዓመቱ የአስፈጻሚ አካላት ዕቅድ ክንውን መገምገምና ግብረ -መልስ መስጠት፣ ጉባኤ ማካሄድ፣ የኦዲት ግኝት ዕዳ አስመላሽ ግብረ-መልስ መስጠት፣ የቀበሌ ምክር ቤቶች በየምክር ቤቶቻቸው ጉባኤ ማካሄድ፣ ለህዝብ ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን እንዲወሰኑ በማድረግ የተሻለ ተግባራትን በበጀት ዓመቱ ተጠናክሮ መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል።
በሌላ በኩል ምክር ቤቱ አብክረው መወያየት ያለበትን ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ በኩል የምክር ቤቱ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባም አፈ ጉባኤው አስገንዝበዋል።
ጉባኤው የ4ኛ ዙር 31ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለጉባኤ መርምሮ ማጽደቅ፣ የምክር ቤቱን 2017 ዕቅድ ክንውን ሪፖርትና የ2018 ዓ/ም ጠቋሚ ዕቅድ መርምሮ ማጽደቅ፣ የወረዳው አስፈፃሚ አካላት የ2017 ዓ/ም ክንውን ሪፓርትና የ2018 ጠቋሚ ዕቅድ መርምሮ ማጽደቅ፣ እንዲሁም 2018 ዓ/ም የበጀት አዋጅና በጀት ረቂቅ መርምሮ ማጽደቅና አዳዲስ የመንግስት ተሿሚዎች ሹመት በመስጠት ጉባዔ ለሁለት ቀን እንደሚመክር ከመርሐ ግብሩ ለማወቅ ተችሎል ።
ዘጋቢ፡ አሸናፊ ግዛው – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ