የትራፊክ አደጋን ከመቀነስና ከመከላከል አኳያ አሽከርካሪዎችና እግረኞች የትራፊክ ህግና- ደንብን መከተልና ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 13/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የትራፊክ አደጋን ከመቀነስና ከመከላከል አኳያ አሽከርካሪዎችና እግረኞች የትራፊክ ህግና- ደንብን መከተልና ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ የአ/ምንጭ ከተማ ነዋሪዎችና አሽከርካሪዎች አሳሰቡ፡፡
አሽከርካሪዎች በተለይም ለእግረኞች ቅድሚያ በመስጠትና የተወሰነውን የፍጥነት ወሰን መጠበቅ እንደሚገባቸው የከተማው ትራፊክ ፍሰት ቁጥጥርና የአደጋ መከላከል ማስተባበሪያ አስታውቋል፡፡
አስተያየታቸውን የሰጠን የከተማው ነዋሪዎች እግረኞች የግራ ጠርዝን ይዞ ከመጓዝ አኳያና በመንገዶች ላይ በእግረኞች ማቋረጫዎችን ተጠቅሞ በመሻገር የትራፊክ አደጋን መከላከል እንደሚቻል አመላክቷል፡፡
አሽከርካሪዎች የተሸከርካሪዎችን አመታዊ እድሳቶችንና የቴክንክ ምርመራዎችን በማድረግ በተለይም እግረኞች በብዛት በሚኖሩባት መሻገሪያዎች ላይ ለእግረኞች ቅዲሚያ መስጠት እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡
ምክትል ኢንስፔክተር ብዙነሽ አመኑ የአ/ምንጭ ከተማ የትራፊክ አደጋ የግንዛቤ ማስጨበጫ ቡድን መሪ ሲሆኑ አደጋን ቀንሶ ከማሽከርከር አኳያ ለአሽከርካሪዎችና ለእግረኞች ሰፊ ግንዛቤ እየሰጠ እንዳለ ጠቁመዋል፡፡
በ2017 በጀት አመት በከተማው የትራፊክ አደጋን ለመከላከልና ለመቀነስ በርካታ ተግባራት መስራታቸውን ምክትል ኮማንደር አዲሳለም እስራኤል የአ/ምንጭ ከተማ ፖሊስ ትራፊክ ፍሰት ቁጥጥርና አደጋ መከላከል ማስተባበሪያ ኃላፊ አስረድተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ስምረት አስማማው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በኮሬ ዞን የአስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች መልሶ የማደራጀት ምክክር መድረክ ተካሄደ
በአጋር ድርጅቶች የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች የመንግስት የልማት ክፍተት በመሙላት የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያላቸው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
በሌማት ትሩፋት ከቤት ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን የምዕራብ አባያ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለፁ