ክልሉን የሠላም ተምሳሌት ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 13/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ክልሉን የሠላም ተምሳሌት ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ አቶ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ አሳሰቡ።
የክልሉ ፀጥታ ምክር ቤት 2ኛ ዓመት 3ኛ ዙር መደበኛ ጉባኤውን በአ/ምንጭ ከተማ አካሂዷል ።
በክልሉ ባለፉት ሁለት ዓመታት ዉስጥ ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከፀጥታው አካላት ጋር በጋራ በመስራት ክልሉን የሠላም ተምሳሌት ለማድረግ የተሠራው ሥራ አበረታች መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ አቶ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለፁ።
በቀጣይም የተጀመረውን የሠላምና የአንድነት ተምሳሌትነት ለማስቀጠልና በ2018 ዓ.ም የታቀዱ ሀገራዊና ክልላዊ አጀንዳዎችን በሠላም እንዲጠናቀቁ በቅንጅት መሰራት እንዳለበትም ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ አሳሰበዋል።
የጸጥታ አካሉን ለማጠናከር የውስጥ አቅሞችን መጠቀም እንደሚገባ ያሳሰቡት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ የጸጥታ አካሉ እና አመራሩ ሠላምን በሠላም ጊዜ መሥራት እንዳለበትም መክረዋል።
በጉባኤው ከክልሉ ሁሉም ዞኖች ሪጂዮ ፖሊ ከተሞች፣ ከፌደራል ፖሊስ እና ክልሉ ጸጥታ አባላት ተሳትፈውበታል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ