ህዝበ ሙስሊሙ ከአካባቢ አልፎ በሀገር አቀፍ ደረጃ አንድነትና ሠላም እንዲረጋገጥ እየሠራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ገለፀ
ምክር ቤቱ በኡለማ ወይም በኃይማኖቱ ሊቃውንት፣ በምሁራን፣ በወጣቶች፣ በሴቶችና በሥራ ማህብረሰብ ዘርፍ በቀጣይ ለአምስት ዓመት የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን የሚመሩ አካላትን ምርጫ ባካሄደበት ወቅት ነው ይህንን የገለፀው።
የኣሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱልቃድር አሊ እንደገለፁት፤ የተመረጡ አካላት የመላው የሙስሊም እምነት ተከታዮች አንድነትንና ሠላምን አጥብቀው የሚሠሩ እንዲሁም ከሌሎች ቤተ እምነቶችም ጋር በመተባበር ከአካባቢ አልፎ ለሀገር መንግስት ሠላምና አንድነት ኃላፊነታቸውን ሊውጡ ይገባል።
የተካሄደው ምርጫም ሰላማዊ፣ ሁሉን ያሳተፈ፣ በግልፀኝነት የተካሄደ ነበር ሲሉም መራጮችና ምርጫውን ያስተባበሩ አካላት ተናግረዋል።
ምርጫው ከከተማ አስተዳደር ወይም ወረዳ ጀምሮ እስከ ፌደራል ድረስ በየደረጃው እየተካሄደ ነሐሴ 30/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ድረስ በተመሳሳይ መልኩ እንደሚጠናቀቅ ሰብሳቢው ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ