ህዝበ ሙስሊሙ ከአካባቢ አልፎ በሀገር አቀፍ ደረጃ አንድነትና ሠላም እንዲረጋገጥ እየሠራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ገለፀ
ምክር ቤቱ በኡለማ ወይም በኃይማኖቱ ሊቃውንት፣ በምሁራን፣ በወጣቶች፣ በሴቶችና በሥራ ማህብረሰብ ዘርፍ በቀጣይ ለአምስት ዓመት የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን የሚመሩ አካላትን ምርጫ ባካሄደበት ወቅት ነው ይህንን የገለፀው።
የኣሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱልቃድር አሊ እንደገለፁት፤ የተመረጡ አካላት የመላው የሙስሊም እምነት ተከታዮች አንድነትንና ሠላምን አጥብቀው የሚሠሩ እንዲሁም ከሌሎች ቤተ እምነቶችም ጋር በመተባበር ከአካባቢ አልፎ ለሀገር መንግስት ሠላምና አንድነት ኃላፊነታቸውን ሊውጡ ይገባል።
የተካሄደው ምርጫም ሰላማዊ፣ ሁሉን ያሳተፈ፣ በግልፀኝነት የተካሄደ ነበር ሲሉም መራጮችና ምርጫውን ያስተባበሩ አካላት ተናግረዋል።
ምርጫው ከከተማ አስተዳደር ወይም ወረዳ ጀምሮ እስከ ፌደራል ድረስ በየደረጃው እየተካሄደ ነሐሴ 30/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ድረስ በተመሳሳይ መልኩ እንደሚጠናቀቅ ሰብሳቢው ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለአካባቢው ማህበረሰብ ለውጥ የሚበጅ፤ ዘመኑን በሚዋጅ የቴክኖሎጂ እውቀት የበለጸጉ ዜጎች የሚፈልቁበት ተቋም ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ
የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጥ የሚገድቡ እንቅፋቶችን በትብብር መፍታት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሀመድናስር ገለጹ