ህዝበ ሙስሊሙ ከአካባቢ አልፎ በሀገር አቀፍ ደረጃ አንድነትና ሠላም እንዲረጋገጥ እየሠራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ገለፀ
ምክር ቤቱ በኡለማ ወይም በኃይማኖቱ ሊቃውንት፣ በምሁራን፣ በወጣቶች፣ በሴቶችና በሥራ ማህብረሰብ ዘርፍ በቀጣይ ለአምስት ዓመት የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን የሚመሩ አካላትን ምርጫ ባካሄደበት ወቅት ነው ይህንን የገለፀው።
የኣሪ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዱልቃድር አሊ እንደገለፁት፤ የተመረጡ አካላት የመላው የሙስሊም እምነት ተከታዮች አንድነትንና ሠላምን አጥብቀው የሚሠሩ እንዲሁም ከሌሎች ቤተ እምነቶችም ጋር በመተባበር ከአካባቢ አልፎ ለሀገር መንግስት ሠላምና አንድነት ኃላፊነታቸውን ሊውጡ ይገባል።
የተካሄደው ምርጫም ሰላማዊ፣ ሁሉን ያሳተፈ፣ በግልፀኝነት የተካሄደ ነበር ሲሉም መራጮችና ምርጫውን ያስተባበሩ አካላት ተናግረዋል።
ምርጫው ከከተማ አስተዳደር ወይም ወረዳ ጀምሮ እስከ ፌደራል ድረስ በየደረጃው እየተካሄደ ነሐሴ 30/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ድረስ በተመሳሳይ መልኩ እንደሚጠናቀቅ ሰብሳቢው ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ